በእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል ግጭት ሊነሳ ይችላል ፣መንግስት ሰራዊቱን ወደ ከተማ እያስገባ ነው

የካቲት 12 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያ ውስጥ በእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል ከፍተኛ ግጭት ሊነሳ ይችላል የሚል ፍርሀት ነግሷል፤ መንግስት ሰራዊቱን በገፍ ወደ ዋና ከተማዋ እያስገባ ነው ባለፉት 8 ሳምንታት ዘወትር አርብ በመቶ ሺ የሚቆጠር ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በአወልያ መስጊድ በመሰባሰብ በነጻነት የማምለክ መብታቸው እንዲከበርላቸው ፣  የሀይማኖት መሪዎቻቸውን በዲሞክራሲያዊ ሁኔታ እራሳቸው እንዲመርጡ እና መንግስት ጣልቃ እንዳይገባባቸው  ሲጠይቁ ቆይተዋል። በአወሊያ የሚሰበሰቡ ሙስሊሞች ...

Read More »

የኢህአዴግ መንግሥት ከተቃዋሚዎች ጋር የሚደረግ የክርክር መድረክ እንዳዘጋጀ እየተናገረ ነው

የካቲት 12 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-‹‹የ ኢህአዴግ መንግሥት ከተቃዋሚዎች ጋር የሚደረግ የክርክር መድረክ እንዳዘጋጀ እየተናገረ ያለው ፤ በአገሪቱ በቂ የፖለቲካ መንቀሳቀሻ ሜዳ አለ በማለት ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማታለል ነው”ሲል በቅርቡ ከፖለቲካ ፓርቶዎች የምክክር መድረክ ራሱን ያገለለው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ገለጸ። የመኢአድ ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ታሪኩ  መኢአድ፤ የፓርቲዎችን የጋራ የምክክር መድረክ ተቀላቅሎ የምርጫ ሥነ ምግባር ደንቡን የፈረመው ‘በፓርቲው ...

Read More »

የታዋቂው ደራሲ ስብሀት ገ/እግዚአብሄር የቀብር ስነ ስርአት ተፈጸመ

የካቲት 12 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የታዋቂው ደራሲ ስብሀት ገ/እግዚአብሄር የቀብር ስነስርአት በቅድስት ስላሴ ካቴደራል ቤተክርስቲያን ተፈጸመ:: ሌቱም አይነጋልኝ፣ትኩሳት፣ሰባተኛው መላክ፣እግረ መንገድ፣አምስት ስድስት ሰባትን በመሳሰሉ ስራዎቹ…የምናውቀው..ለኢትዮጵያ ስነ ፅሁፍ ታላላቅ ስራዎችን ያበረከተው ጋዜጠኛና ደራሲ ስብሃት ገብረእግዚአብሔር ከዚህ አለም በሞት ተለየ፡፡ በፍልስፍና ጽሁፍ እና እንዲሁም የግልጽ የአጻጻፍ ዘይቤው በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ እውቅና ያለው እና በጸሃፊነት ለረጂም ዘመናት የቆየው ስብሃት ገ/እግዚአብሄር ከዚህ አለም በሞት ...

Read More »

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሀይማኖት አባቶች መካከል ለቀናት በርቀት ሲካሔድ የቆየው የርቀ ሰላም ድርድር ዛሬም መቀጠሉን መረዳት ተችሏል::

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሀይማኖት አባቶች መካከል ለቀናት በርቀት ሲካሔድ የቆየው የርቀ ሰላም ድርድር ዛሬም መቀጠሉን መረዳት ተችሏል::

Read More »

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የስልጣን መልቀቂያ አስገቡ

የካቲት 10 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከወራት በፊት በዳውሮ ዞን ዋካ ከተማ ለተነሳው ጥያቄ መንግስት ችግሩን ከመፍታት ይልቅ ተቃውሞ የሚያነሱ ሰዎችን ማስፈራራት፣ የስልጣን ቦታዎችን ለመንግስት ታማኝ በሆኑ ሰዎች ማስያዝ መምረጡን የአካባቢው ሰዎች ይናገራሉ። የመንግስት እና የህዝቡን ፍላጎት ለማጣጣም አልቻልኩም በማለት የስልጣን ጥያቄ ያቀረቡት አቶ እስራኤል ኦታሮ ፣ በአካባቢው ያለውን ችግር ለመፍታት የክልል ባለስልጣኖች ፍላጎት የሌላቸው በመሆኑ ወደ ሙያየ ተመልሼ ህዝቡን ...

Read More »

አንዳንድ ሙስሊሞች የማስፈራሪያ መልእክት እየደረሳቸው መሆኑን ለኢሳት ተናገሩ

የካቲት 10 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-አንዳንድ ሙስሊሞች የግንቦት7፣ የኤርትራ መንግስት፣ የአልሸባብና የአልቃይዳ ወኪሎች መሆናችሁ ተደርሶባችሁዋል  የሚል መልእክት እየደረሳቸው መሆኑን ለኢሳት ተናገሩ ድምጻቸው ወይም ምስላቸው እንዳይወጣ የጠየቁት ሙስሊሞች በአወልያ መስጊድ ለተገኘው ዘጋቢያችን የደረሰባቸውን ማስፈራሪያና ዛቻ አጫውተውታል። አንድ የ25 አመት ወጣት ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ባለፈው ሳምንት ከስግደት ሲመለስ፣ ” የምትሰራውን ደርሰንበታል፣ ከእነማን ጋር እንደምትገናኝ ዝርዝር መረጃ እጃችን ላይ አለ። እንቅስቃሴህን ባታቆም ...

Read More »

ፍትህ የአቦይ ስብሀት ንግግር የድርጅቱ አቋም እንደሆነና እንዳልሆነ ግልፅ እንዲደረግ ጠየቀች

የካቲት 10 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ህወሀት ዛሬ በሚያከብረው 37 ኛ ዓመት በዓሉ ላይ፤ የቀድሞው የድርጅቱ ሊቀ-መንበር አቦይ ስብሀት ነጋ በቅርቡ በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ቀርበው የአክሱም ታሪክ እንኳን ሌላውን ኢትዮጵያ፤ ከትግራይም አጋሜንና ተንቤንን አይመለከትም ማለታቸው፤ የድርጅቱ አቋም እንደሆነና እንዳልሆነ ግልፅ ያደርግ ዘንድ ፍትህ ጋዜጣ ጠየቀች። ፍትህ ይህን ጥያቄ ያቀረበችው፤የድርጅቱን 37 ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በማስመልከት  በህወሀት ዙሪያ አቋሟን ባንፀባረቀችበት መልዕክት ...

Read More »

በኦሞ ሸለቆ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች ህይወታቸው አሣሳቢ አደጋ ውስጥ ወድቋል ተባለ

የካቲት 10 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በታችኛው ኦሞ ሸለቆ  አካባቢ የሚኖሩ 200 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች መሬታቸው ለህንድ ኩባንያዎች በመሰጠቱ ህይወታቸው አሣሳቢ አደጋ ውስጥ መውደቁን አልጀዚራ ዘገበ። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ የ አካባቢው ነዋሪዎች  መሬታቸው “ለልማት ይፈለጋል”ተብለው በግዳጅ ከቀያቸው እየተፈናቀሉ ሲሆን፤ ቤታችንን እና ይዞታችንን አንለቅም ያሉ ደግሞ እየታሰሩ ነው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩት እነዚህ ዜጎች እየተፈናቀሉ ያሉት፤ የኢትዮጵያ መንግስት በህንድ ...

Read More »

አቶ አንዱዓለም አራጌ በማረሚያ ቤት ድብደባ ተፈጸመበት

 የካቲት 9 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሽብርተኝነት ስም በእስር ላይ የሚገኘው የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆነው  አቶ አንዱአለም አራጌ ቃሊቲ በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ በተቀመጠበት የካቲት 7 ቀን 2004ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት አካባቢ ተደብድቧል፡፡ ከድብደባ በሁዋላ ፊቱ ላይ ጠባሳ የሚታይ ሲሆን ጭንቅላቱ አካባቢም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ አቶ አንዱአለም ለወንድሙ አቶ አብርሀም አራጌ በብስጭት እንደነገሩት በማረሚያ ቤቱ የተቀነባበረና ...

Read More »

በጋምቤላ ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት ተገደሉ

የካቲት 9 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ላለፉት ጥቂት ቀናት መረጋጋት የሰፈነበት ይመስል የነበረው የጋምቤላ ክልል ከትናንት ሁሙስ የካቲት ስምንት ቀን ከሰአት ጀምሮ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደሚገኝ ምንጮች ገልጠዋል። ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላትና አንድ ሲቪል ሰራተኛ በላንድ ክሩዘር መኪና ከዋና ከተማዋ ጋምቤላ ተነስተው 70 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ወደ ሚገኘው የ አበቦ ወረዳ በማምራት ላይ ሳሉ ሁለት የፌደራል ፖሊስን የደንብ ልብስ የለበሱ ...

Read More »