ግንቦት 20 ከትግራይ ክልል በቀር በሌሎች አካባቢዎች ሳይከበር ቀረ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 20/2011)ግንቦት 20 ከትግራይ ክልል በቀር በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች አለመከበሩ ታወቀ። ከ28 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓሉ ሳይከበር መቅረቱን የተለያዩ የዜና አውታሮች ዘግበዋል። በትግራይ አክሱም በተከበረው የግንቦት 20 በዓል የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካዔል በግንቦት 20 የተገኘው ድል ባለፉት አራት ዓመታት እየተሸረሸረ መጥቷል ሲሉ መግለጻቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ግንቦት 20ን አስመልክተው ያለፈ ቁስላችንን እየነካካን ...

Read More »

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተሳሳተው ካርታ ይቅርታ ጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 20/2011) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ ገጹ ለተጠቀመው የተሳሳተ ካርታ ይቅርታ ጠየቀ። ሶማሊያን የኢትዮጵያ አካል አድርጎ በወጣው ካርታ በመላው ዓለም የሚገኙ ሶማሊያውያን ተቃውሞ አሰምተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የተሳሳተውን የአፍሪካ ካርታ ከድረገጹ እንዲወርድ መደረጉን ገልጸው ሁኔታው እንዴት እንደተከሰተ በማጣራት ላይ ነን ብለዋል። ካርታው ከሶማሊያ ሌላ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራትንም ድንበሮች በተሳሳተ መልኩ ...

Read More »

በኦነግ ስም የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ህገወጥ ተግባራትን እንደሚያከናውኑ ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 20/2011)በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ዝርፊያን ጨምሮ የተለያዩ ህገወጥ ተግባራትን የሚያከናውነው ኦነግ ሳይሆን በኦነግ ስም የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ናቸው ሲል የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አስታወቀ። በኦነግ ትዕዛዝ ስር የሚተዳደር ወታደራዊ ሃይል የለኝም ሲል ግንባሩ ገልጿል። የኦነግ ቃል አቀባይ አቶ ቶሌራ አደባ ለመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ በዘጡት ቃለመጠይቅ እንደገለጹት ኦነግ ታጣቂ ሃይሎቹን ለአባገዳዎች አስረክቦ በሰላማዊ መንገድ ትግሉ ቀጥሏል። በኦነግ ስም በዘረፋ ተግባር የተሰማሩት ...

Read More »

በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ አምስት ተማሪዎች በቁጥጥር ስር

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 20/2011)በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ከአንድ ተማሪ ግድያ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ አምስት ተማሪዎች በቁጥጥር ስር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያ የህዝብ ግንኙነት ክፍል አስተባባሪ ኢንስፔክተር ጎበዜ ይርሳው ለኢሳት እንደገለጹት በግንቦት 16ቱ ግድያ የተጠረጠሩትና በድንጋይ ውርወራው እንዳሉበት የተደረሰባቸው አምስቱ ተማሪዎች ላይ ፖሊስ ምርመራ እያደረገ ነው። ተማሪውን ለግድያ ያበቃው ምክንያትንም በተመለከተ ምርመራ በመደረግ ላይ ነው ያሉት ኢንስፔክተር ...

Read More »

ሳዑዲ ለኢትዮጵያውያን የሰጠችውን ቪዛ ሰረዘች

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 18/2011)ሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገሯ ለስራ ለሚገቡ ኢትዮጵያውያን የሰጠችውን ቪዛ መሰረዟን አስታወቀች። የሳዑዲ አረቢያ የስራና ሰራተኞች ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ቪዛው የተሰረዘው ከኢትዮጵያ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በስራ ቅጥር ላይ ስምምነት ባለመደረሱ ነው። ከረመዳን ጾም መግባት አስቀድሞ ሳዑዲ አረቢያ መድረስ ያለባቸው በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ስምምነት ባለመደረሱ ምክንያት መቅረታቸው ታውቋል። ሳዑዲ አረቢያ በቅጥር ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ሰፊ ልዩነት መኖሩን ከመግለጽ ...

Read More »

በቴፒ በነዋሪዎች ላይ የሚደርሰው እስርና ግድያ እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 19/2011) በቴፒ በነዋሪዎች ላይ የሚደርሰው እስርና ግድያ አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ይህን ተከትሎም በአካባቢው ጭንቀትና ውጥረት መንገሱን ነው ነዋሪዎች ለኢሳት የገለጹት። የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ምርመራ ቡድን በአካባቢው እንቅስቃሴ እየደረገ ቢሆንም ለውጡን ያልተቀበሉ አመራሮች እጃቸው በወንጀሉ ውስጥ መኖሩ ሁኔታውን አስቸጋሪ አድርጎታል ብለዋል። በደቡብ ክልል ከፋ ዞንን ጨምሮ በሶስት ዞኖች ከመጋቢት 20 ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ የአስቸኳይ ...

Read More »

የአሃዱ ሬዲዮ ባልደረባ ጋዜጠኛ ታምራት አበራ ተፈታ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 18/2011)በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ለእስር የተዳረገው የአሀዱ ሬዲዮ ባልደረባ ጋዜጠኛ ታምራት አበራ በዛሬው ዕለት ተለቀቀ። ባለፈው ዓርብ ከሚሰራበት ቦታ ተይዞ ወደ ሰንዳፋ ተወስዶ  የታሰረው  ጋዜጠኛ ታምራት በዋስ መለቀቁን የአሀዱ ሬዲዮ ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ሊዲያ አበበ ለኢሳት ገልጻለች። እሷን ጨምሮ ሌሎች የጣቢያው ባልደረቦችም የፊታችን ረቡዕ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ የቃል መጥሪያ እንደደረሳቸውም ያገነኘው መረጃ ያመለክታል። ከአንድ ወር በፊት በተሰራ ዘገባ ...

Read More »

በሶማሌ ክልል ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ ግለሰቦች ተላልፈው እንዲሰጡ ተጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 18/2011)በሶማሌ ክልል የጅምላ ግድያን ጨምሮ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ ግለሰቦችን አሳልፈው እንዲሰጡ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ንግግር  መጀመሩ ተገለጸ። በሶማሌ ክልል የሚገኘው አሰቃቂ እስር ቤት  ጄል ኦጋዴን  ሃላፊም ጎረቤት ሃገር ሶማሊያ ውስጥ በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ባለፈው ቅዳሜ የጄል ኦጋዴን ሃላፊ የነበሩት ግለሰብ በሶማሊያ ውስጥ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከጎረቤት ሶማሊያ   መንግስት ጋር  በተደረገ  ትብብር መሆኑንም መረዳት ተችሏል። የሶማሌ ክልል ...

Read More »

ማህበረ ግዮራን ዘረኢትዮጵያ ዘጠኝ ኢትዮጵያዊያን ሴቶችን ሊሸልም ነው

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 16/2011)ሲድ የተባለው በአሜሪካ የሚገኝ የሽልማት ድርጅት ዘጠኝ ኢትዮጵያዊያን ሴቶችን በክብር ሊሸልም መሆኑን አስታወቀ። ማህበረ ግዮራን ዘረኢትዮጵያ (ሲድ) ተብሎ የሚታወቀው ተቋም ለወደፊት ተስፋ የተጣላባቸውን ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ይሸልማል። ከተሸላሚ ሴቶች መካከል የጠቅላይ ፍርድቤት ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ማአዛ አሸናፊ፥አትሌት ኮለኔል ደራርቱ ቱሉ እና ወ/ሮ የትነበርሽ ንጉሴም ይገኙበታል። የማህበር ግዮራን ዘረ ኢትዮጵያ(ሲድ) 27ኛ አመት የክብር ሽልማት የሚካሄደው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ግንቦት 26/2019 ዓ.ም ...

Read More »

የፌደራል ፖሊስ የእነ አቶ ጌታቸው አሰፋን መጥሪያ ማድረስ አልቻልኩም ሲል ገለፀ

 (ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 21/2011)የፌደራል ፖሊስ በሌሉበት ጉዳየቸው እየታየ ያለው እነ አቶ ጌታቸው አሰፋ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ የተሰጠው የመጥሪያ ትዕዛዝ በጊዜ ከፍርድ ቤት ባለመውጣቱ ማድረስ አልቻልኩም ሲል ገለፀ። የፌደራል ፖሊስ ትዕዛዙ የተሰጠው ግንቦት ስምንት ቢሆንም የመጥሪያ ትዕዛዙ ከፍርድ ቤት የወጣው ግንቦት 14 በመሆኑ ትግራይ ክልል ድረስ ሄዶ ለተከሳሾች ለማድረስ የጊዜ ዕጥረት አጋጥሞኛል ብሏል። የቀድሞው የደህንነት ሐላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ የተከሰሱ ...

Read More »