በምዕራብ ጉጂ ሰባት ሰዎች ተገደሉ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 14/2011)በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ሰባት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ። በምዕራብ ጉጂ ልዩ ስሙ ደራራ በሚባል አካባቢ በተፈጸመ ጥቃት የተገደሉት ሰላማዊ ዜጎች መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ባለፈው ሳምንትም ሀረቀሎ በተባለ ቦታ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል። ጥቃቱን የኦነግ አባላት ናቸው በተባሉ ታጣቂዎች መከላከያ ሰራዊት ላይ ተኩስ መከፈቱን ተከትሎ የመንግስት ወታደሮች በወሰዱት ርምጃ ሰላማዊ ዜጎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ጥቃቱ በየጊዜው ...

Read More »

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዝርፊያ ጋር በተያያዘ አንድ ናይጄሪያዊ ባለሀብት ታሰሩ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 12/2011)ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተዘረፈ ከ1ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ ዶላር ጋር በተያያዘ አንድ ናይጄሪያዊ ባለሀብት መታሰራቸው ተገለጸ። የሲንጋፖር ፍርድ ቤት ባለፈው ሃሙስ ባዋለው ችሎት ቋሚ የመኖሪያ አድራሻ ያላቸውና በሲንጋፖር የሚኖሩት ናይጄሪያዊ ባለሀብት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገንዘብ እንዲሸሽ አድርገዋል በሚል ክስ የሶስት ዓመት እስር በይኖባቸዋል። ገንዘቡን በተለያዩ የብሔራዊ ባንክ ሃላፊዎች ፍቃድ በመውሰድ ለናይጄራዊው ባለሀብት ሲያስተላለፉ ነበሩ የተባሉት ጓደኛቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ...

Read More »

የጸረ ሽብር ህጉ እንዲሻሻል ውሳኔ ተሰጠ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 12/2001) የሚኒስትሮች ምክር ቤት የጸረ ሽብር ህጉ በዜጎች መብትና ነጻነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳደረ ነው በማለት እንዲሻሻል ውሳኔ ሰጠ። ባለፈው ቅዳሜ የተሰበሰበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ2001 የጸደቀው የጸረ ሽብር ህግ የይዘትና የአፈጻጸም ክፍተቶች ያሉበት በመሆኑ እንዲሻሻል ውሳኔ አቅርቧል። ህጉ የአለምን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ ረቂቅ አዋጅ እንዲሻሻል ምክር ቤቱ ወስኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መላኩን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ...

Read More »

ከምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር ሸሽተው ሱዳን የገቡ ኢትዮጵያውያን ተመለሱ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 12/2011)በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር በተከሰቱ ግጭቶች ሽሽተው ሱዳን ከገቡ ኢትዮጵያውያን መካከል 1500 የሚሆኑትን ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ማድረጉን የመከላከያ ሰራዊት አስታወቀ። የሰራዊቱ 33ኛ ብርጌድ እንዳስታወቀው በቅርቡ በአካባቢዎቹ ተከስተው የነበሩትን ግጭቶች ተከትሎ ወደ ሱዳን የገቡ ኢትዮጵያውያንን ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ የማድረጉ ስራ እየተካሄደ ነው። የብርጌዱ አዛዥ ብርጋዲየር ጄነራል ዓለሙ አየለ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ሌሎች ኢትዮጵያውያንንም ለማስመለስ ሰራዊቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ...

Read More »

ከኢትዮጵያ የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር መጨመሩ ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 12/2011) ከኢትዮጵያ ወደ ተለያዩ የውጭ ሃገራት፣ ከገጠር ወደ ከተማና ከክልል ወደ ክልል የሚሰደዱ ሰዎች ብዛት መጨመሩን እና  ከፍተኛ መሆኑ መረጋገጡን  በምሥራቅና በደቡብ አፍሪካ የማህበራዊ ሳይንስ ምርምር ተቋም አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ላለፉት አምስት ዓመታት ባደረገው ምርምር ስደትን ሕግ በማውጣትና ድንበርን በመዝጋት ማስቆም እንደማይቻል አረጋግጭላሁ ብሏል። ‹‹በኢትዮጵያ ስደትን የሚያመቻቹ የተለያዩ አካላት›› በሚል ርዕሰ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የምርምሩ ባልደረባና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ...

Read More »

አንዳንድ የአዴፓ አመራሮች በሚከሰቱ ግጭቶች በቀጥታና በተዘዋዋሪ እጃቸው አለበት ሲል ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 12/2011)በአማራ ክልልና በአጎራባች አካባቢዎች በሚከሰቱ ግጭቶች አንዳንድ የአዴፓ አመራሮች በቀጥታና በተዘዋዋሪ እጃቸው አለበት ሲሉ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ገለጹ። ፕሬዝዳንቱ ዶክተር አምባቸው መኮንን ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቆይታ ግጭቶቹን ተከትሎ በተደረጉ ግምገማዎች የፓርቲ አንዳንድ አመራሮች በማባባስና ሰላም እንዳይፈጠር ማድረጋቸው ተደርሶበታል ብለዋል። በአማራ ክልል የተስፋፋውን የህገወጥ መሳሪያ ዝውውር ለማስቆም በየአካባቢው የፍተሻ ኬላዎችን በማቋቋም የመከላከል ስራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል ዶክተር አምባቸው። ጽንፍ ...

Read More »

ግሎባል አሊያንስ ለሀገር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 9/2011)የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ግሎባል አሊያንስ እያደረገ ያለውን ሀገራዊ አስተዋጽኦ ታላቅ ተግባር ነው ሲሉ አወደሱት። ዓለም ዓቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት ግሎባል አሊያንስ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ ጋር ውይይት አደረገ። ባለፈው ረቡዕ ለጌዲዮ ተፈናቃዮች የ31 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ያደረገው ግሎባል አሊያንስ በውጭ በሚገኙ ኢትዮጵያውያንና በመንግስት መካከል መልካም ግንኙነት እንዲኖር የሚያስችል እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጿል። የግሎባል አሊያንስ የኢትዮጵያ ...

Read More »

በኤሌክትሪክ መቆራረጥ የተነሳ ከፍተኛ ችግር ውስጥ መግባታቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 9/2011)በኤሌክትሪክ መቆራረጥ የተነሳ ከፍተኛ ችግር ውስጥ መግባታችውን በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች ገለጹ። መንግስት የኤሌክትሪክ አገልግሎትን በፈረቃ ሊያደርገው መሆኑን ዛሬ አስታውቋል። ኢሳት ያነጋገራቸው በሀዋሳ፣ በአዲስ አበባ፣ በባህርዳርና አዳማ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች ሰሞኑን የተከሰተው የሃይል መቆራረጥ ያልተለመደ በመሆኑ ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን ገልጸዋል። የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሃይል መቆራረጡ የተከሰተው በግድቦች በቂ ውሀ ባለመኖሩ ምክንያት የተፈጠረ ነው ብሏል። ችግሩ ለሱዳንና ለጅቡቲ ...

Read More »

የህክምና ባለሙያዎች የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 9/2011)በተለያዩ ከተሞች በህክምና ባለሙያዎች የተቃውሞ ሰልፎች ተደረጉ። መንግስት ጥያቄችንን ለመፍታት ዝግጁ አይደለም በሚል በአዲስ አበባ፣ በደብረማርቆስ፣ በአክሱምና በሌሎች ከተሞች ተቃውሞ ሰልፎች መካሄዳቸውን የደረሰን መረጃ ያመልክታል። በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አንዳንድ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች የተካሄደው አድማ ለሶስተኛ ቀን ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር አድማው ተገቢ አይደለም ሲል መግለጫ ሰጥቷል። የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር አሚር አማን መመለስ የምንችለውን እየመለስን ነው፣ ከጥቅማጥቅሞች ...

Read More »

የወላይታ ሕዝብን ጥያቄ ያስተናገደው ሕዝባዊ ሰልፍ በሰላም ተጠናቀቀ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 9/2011)በወላይታ ሶዶ የተካሄደውና የወላይታ ሕዝብን ጥያቄ ያስተናገደው ሕዝባዊ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁ ተገለጸ። ሰልፈኞቹ የክልል እንሁን ጥያቄን ጨምሮ ባለ አምስት ነጥቦችን የያዘ ጥያቄን ለሚመለከተው አካል ማቅረባቸውን ገልጸዋል። ሰልፈኞቹ ለኢሳት እንዳሉት ማንነትን መሰረት አድርጎ በወላይታ ህዝብ ላይ የሚደርሰው ጥቃት ይቁም፣ወንጀለኞች ለህግ ይቅረቡ የሚሉና ሃገራዊ ለውጡ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የህግ የበላይነት ይከበር የሚሉ መልዕክቶች ተላልፈዋል። የወላይታ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀመንበር ዶክተር ብስራት ...

Read More »