ኢትዮጵያ በህንድ ባንጋሎሬ የቆንሱላ ጽ/ቤት ከፈተች

የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያ በህንድ ባንጋሎሬ የቆንሱላ ጽ/ቤት ከፈተች፤ የካራቱሪ ዲሬክተር የቆንሱላዉ የክብር ተጠሪ ሆነዉ ተሾሙ የኢትዮጵያ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በደቡባዊ ህንድ ካርና-ታካ ክልል ኢንቬስትሜንትን ለማስፋፋት የሚረዳ የቆንሱላ ጽ/ቤት መክፈቱን ሂንዱ ቢዝነስ የመረጃ መረብ ገለፀ። የጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ሃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ሙክታር ከዲር የቆንሱላ ጽ/ቤቱ የተከፈተዉ አቅም በፈቀደ ተገቢዉን ቴክኖሎጂና የሰለጠነ ሃይል ለመጠቀም፤ እንዲሁም አረንጓዴዉን አብዮት ...

Read More »

ሁለትን የስዊድናዊ ጋዜጠኞች ለማስፈታት የተጀመረዉ ዉይይት በመጠናቀቅ ላይ ነው

የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በኢትዮጵያ በእስር ላይ ያሉትን ሁለት ስዊድናዊ ጋዜጠኞችን ለማስፈታት የተጀመረዉ ዉይይት በመጠናቀቅ ላይ እንዳለ ተገለፀ የአዉሮፓ ፓርላማ አባልና የቀድሞ የቤልጅየም የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉዊስ ሚቼል ከጠ/ሚኒስትር መለስ ጋር ያደረጉት ዉይይት ጠቃሚ እንደነበር በመግለፅ ሁለቱ ስዊድናዊ ጋዜጠኞች ማርቲን ሺቤ እና ጆሃን ፔርሰን በቅርብ ቀናት ዉስጥ ከእስር እንደሚፈቱ ተናግረዋል።  ሁለቱ ስዊድናዊ ጋዜጠኞች በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ በመግባትና ...

Read More »

ደራሲ፣ ጋዜጠኛና ተርጓሚ ማሞ ውድነህ አረፉ

የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-53 መፅሃፍትን ለህዝብ ያበረከቱት ታላቁ ደራሲ  ጋዜጠኛና ተርጓሚ ማሞ ውድነህ  በ77 አመታቸውነው ያረፉት። ደራሲ ማሞ ከጦርነት እና ከስለላ ጋር በተያያዘ የተረጎሙዋቸው ስራዎች በብዙ አንባቢያን ዘንድ እንዲወደዱ አድርጓቸዋል። የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር  ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው በለጠ የጤና ጥበቃው ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሀኖም  አንጋፋው ደራሲ ማሞ ውድነህ በጠና መታመማቸውን ተከትሎ የነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ እንዲመቻችላቸው ለሚኒስትሩ ያቀረቡት ጥያቄ ...

Read More »

ቤተ እስራኤላዊዋ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ሆነዉ ተሾሙ

የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የእስራኤል የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቤተ እስራኤላዊዋ በላይነሽ ዜቫዲያን በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ሆነዉ እንዲያገለግሉ መሾሙ ተገለፀ። ከ28 አመታት በፊት በቤተ እስራኤላዊነት ወደ ቅድስቷ አገር የተጓዙት የ44 አመቷ ወ/ሮ በወጣትነት እድሜያቸዉ ወደ ተለዩዋት ሃገራቸዉ በአምባሳደርነት መመለሳቸዉ የሚሰጣቸዉን ደስታ በመግለፅ የሳቸዉ ለዚህ ስልጣን መታጨት እስራኤል ለነባር ዜጎቿም ሆነ ለአዲስ ስደተኞች እኩል እድል እንደምትሰጥ ያረጋግጣል ብለዋል።  ___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________ ESAT ...

Read More »

የሱዳን የመከላከያ ሚኒስትር ላይ የእስር ትእዛዝ ወጣባቸው

 የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የሱዳን የመከላከያ ሚኒስትር አብደል-ራህም መሃመድ ሁሴን በሱዳን ዳርፉር ግዛት በፈፀሙት የጦር ወንጀል እንዲጠየቁ አለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የእስር ትእዛዝ ማዉጣቱን የአሜሪካን ድምፅ ዘገበ። የእስር ትእዛዙን የሰጠዉ ፍርድ ቤት ሚኒስትሩ በግድያ፤ በአስገድዶ መድፈር፤ በሰዎች ላይ አሰቃቂ ድብደባና ስቃይ በማድረስና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ባደረሱት በደል በጠቅላላዉ በ41 ወንጀሎች እንደሚጠየቁ ገልጿል። ከዚህ ሌላ ግለሰቡ በነሃሴ 2003 ...

Read More »

በመላ አገሪቱ የጤፍ ዋጋ በከፍተኛ በአስፈሪ ሁኔታ እየናረ ነው

የካቲት 22 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአማራ ፣ በድሬዳዋ፣ በአዲስ አበባና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ያሉትን የኢሳት ምንጮች በማናገር ለማረጋገጥ እንደተቻለው የጤፍ እና የአንዳንድ የእህል ምርቶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። በባህርዳር እና አካባቢዋ ለወትሮው 1 ሺ ብር ይሸጥ የነበረው ነጭ ጤፍ ዛሬ 1300 ብር  ሲጨጥ ውሎአል። በድሬዳዋ ደግሞ 1ሺ ብር የነበረው ጤፍ እስከ 1250 ብር በመሸት ላይ ነው። በአዲስ አበባም እንዲሁ ...

Read More »

መንግስት ባልተጠና የእርከን ስራ ህዝቡን እያማረረው ነው ተባለ

የካቲት 22 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት የደቡብ፣ አማራ እና ድሬዳዋ ዘጋቢዎች እንደገለጡት መንግስት ህዝቡን ለመቆጣጠር በቀየሰው አንድ ለአምስት አደረጃጀት በመጠቀም ፣ አርሶአደሩን እና በተለያዩ ወረዳዎች የሚኖሩ ዜጎችን በግዳጅ በሳምንት ለሶስት ቀናት የእርከን ስራ እንዲሰሩ እያደረገ ነው። አርሶአደሩ እንዳሉት እርሳቸው በሚሩበት በቦረና ዞን የተለያዩ ቀበሌዎች በርካታ ሰዎች ታስረው መገኘታቸውን በዝርዝር ገልጠዋል አንድ ስማቸው እንዳይገለጥ የጠየቁ የግብርና ባለሙያ እንደተናገሩት ከሶማሊ ክልል ...

Read More »

ኢትዮጵያ አንድ ነባር የህወሀት አባል የደቡብ ሱዳን አምባሳደር አድርጋ ሾመች

የካቲት 22 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ አዲሱ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት ፍሬ ተስፋ ሚካኤል ተስፋጽዮን የተባሉ ነባር የህወሀት አባል ናቸው። የሰሜን ሱዳን አምባሳደር ሆነው ከወራት በፊት የተሾሙት አባዲ ዘሙ ነባር የህወሀት አባል ሲሆኑ ፣ አሁንም ከአንድ ብሄርና ከአንድ ድርጅት የመጡ ሰው በተመሳሳይ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ሆነው መሾማቸው የመለስ መንግስት በሱዳን የሚካሄደውን እንቅስቃሴ ምን ያክል ለመቆጣጠር እንደፈለገ ያሳያል ሲሉ ...

Read More »

መንግስት የአወልያን ሰላማዊ ተቃውሞ ወደ ግጭት ለመለወጥ እየጣረ ነው ተባለ

የካቲት 22 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአወሊያ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና በትምህርት ቤቱ አስተዳደር መካከል ተከስቶ ወደ ብዙሀኑ ሙስሊም የተሸጋገረውና  ስምንት ሳምንታት  ያስቆጠረው ተቃውሞ  መፍትሔ ሳያገኝ፤ ይልቁንም ውሎ ሲያድር እየጋለና እየተጋጋመ መጥቶ እጅግ አሣሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል። ብዙሀኑ ሙስሊሞች ሳምንታት በዘለቀው ተቃውሟቸው   የሙስሊሙን ህብረተሰብ እንዲመሩ በነሱ ምርጫ ሳይሆን በመንግስት ውክልና የተቀመጡት የመጂሊስ አመራሮች እንዲነሱላቸው እንዲሁም፤  መንግስት ፦“አህባሽ” የተሰኘውንና ከውጪ የመጣ ነው ...

Read More »

የአማራ ተወላጆች ከደቡብና ኦሮሚያ ክልሎች ለቀው እየወጡ ነው

የካቲት 21 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአማራ ተወላጅ አርሶአደሮች ከደቡብና ኦሮሚያ ክልሎች ለቀው እየወጡ ነው፣ በአርሶአደሮች ላይ ዘግናኝ ደርጊትም እየተፈጸመባቸው ነው በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች ለረጅም አመታት ይኖሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች ከክልሎች ነቅለው እንዲወጡ እየተገደዱ መሆኑንና በርካታ አርሶአደሮች ለዘመናት ያፈሩትን ሀብትና ጥሪት እየተነጠቁ ለስቃይ እየተደራጉ መሆኑን አንድ የመኢአድ የአመራር አካል ለኢሳት ተናግረዋል። አቶ ያሬድ ግርማ ለኢሳት እንደገለጡት በሁለቱ ክልሎች የሚገኙ የአማራ ...

Read More »