ኢትዮጵያ በህንድ ባንጋሎሬ የቆንሱላ ጽ/ቤት ከፈተች

የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያ በህንድ ባንጋሎሬ የቆንሱላ ጽ/ቤት ከፈተች፤ የካራቱሪ ዲሬክተር የቆንሱላዉ የክብር ተጠሪ ሆነዉ ተሾሙ

የኢትዮጵያ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በደቡባዊ ህንድ ካርና-ታካ ክልል ኢንቬስትሜንትን ለማስፋፋት የሚረዳ የቆንሱላ ጽ/ቤት መክፈቱን ሂንዱ ቢዝነስ የመረጃ መረብ ገለፀ።

የጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ሃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ሙክታር ከዲር የቆንሱላ ጽ/ቤቱ የተከፈተዉ አቅም በፈቀደ ተገቢዉን ቴክኖሎጂና የሰለጠነ ሃይል ለመጠቀም፤ እንዲሁም አረንጓዴዉን አብዮት ለማስተናገድ  መሆኑን አመልክተዋል።

አቶ ሙክታር በተጨማሪ የህንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ከሚገኙት በቁጥር ከፍተኛ ከሆኑት የዉጭ ኢንቬስተሮች  አንዱ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

በተከፈተዉ ቆንስላ ዉስጥ ህንዳዊዉ የካራቱሪ ግሎባል ዲሬክተር ሚ/ር ሳይ ራም-ክሪሽና ካራቱሪ  የክብር ተጠሪ ሆነዉ ተሹመዋል።  

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide