አወልያ መስጊድ ታህሪር አደባባይ ሆኖ መዋሉ ተዘገበ

የካቲት 9 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት ዘጋቢ እንደገለጠው በዛሬው እለት በአወልያ መስጊድና በዙሪያው ባሉ ቦታዎች ከ100 ሺ ያላነሰ ህዝብ ተገኝቷል ከሙስሊሙ የተወከሉ ሰዎች ባለፈው ሰኞ ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር ያደረጉትን ውይይት ሪፖርት ለመስማማት ህዝቡ አሰፍስፎ ይጠብቅ ነበር፡፡ ተወካዮቹ የህዝቡን ስሜት በመረዳት የመንግስት ባለስልጣናት ጥያቄያቸውን እንደተቀበሉዋቸው እና የመጨረሻ መልስ ለመስጠት ለየካቲት 26 ቀነ ቀጠሮ እንደሰጧቸው ተናግረዋል። በርካታ ወጣቶች ተወካዮች በሰጡት መልስ ...

Read More »

የአቤ ቶኪቻው ወንድም የሆነው ወንደሰን ጌታነህ አንድ ሆቴል ውስጥ ሞቶ ተገኘ

የካቲት 9 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የጸሀፊና ሀያሲ አቤ ቶኪቻው የሶስት ጊዜ ታናሽ ወንድም የሆነው ወንደሰን ጌታነህ ሰሜን መዘጋጃ አካባቢ ከሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ ሞቶ ተገኘ፡፡ ተመስገን ደሳለኝ በፌስ ቡኩ ላይ ባስቀመጠው ዘገባ እንዲህ ብሎአል “ይህ ልጅ ገና ታዳጊ ነው፡፡ በአንድ ገራዥ ውስጥም በብየዳ ሙያ ተሰማረቶ ይሰራል፡፡ ገነት ሆቴል አካባቢም ብቻውን ተከራይቶ ይኖር ነበር፡፡ ስለድንገተኛ አሟሟቱ ፖሊስ መረጃ ለመስጠት ጊዜው ...

Read More »

የኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮች በኦጋዴን 16 ሰላማዊ ዜጎችን መግደላቸዉ ተገለፀ

የካቲት 9 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በደቡብ ምስራቅ ኦጋዴን በደገሃቡር ጉነ-ጋዶ አካባቢ የኢትዮጵያ መንግሰት ወታደሮች በመንገድ ዳር ሰብሰብ ብለዉ ይነጋገሩ በነበሩ ሰላማዊ ነዋሪዎች ላይ በከፈቱት ተኩስ 16 ሰዎች መግደላቸዉን የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር መግለፁን ብሉምበርግ የዜና ወኪል ገልጿል። በወቅቱ ነዋሪዎቹ በመነጋገር ላይ የነበሩት ከአንድ ቀን ቀደም ብሎ በአካባቢዉ ነዋሪ በሆኑ አንድ አረጋዊና አንድ የፖሊስ ኮሚሽነር ላይ ስለተፈፀመዉ ግድያ እንደነበር የዜና ...

Read More »

የአዉሮፓ ህብረት ሁለቱ ስዊድናዉያን እንዲለቀቁ ጠንካራ ጫና በማድረግ ላይ ነው

የካቲት 9 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ስዊድን አባል የሆነችበት አንድ የአዉሮፓ ህብረት የልኡካን ቡድን በሽብርተኝነት ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዉ ባለፈዉ መስከረም እስራት የተፈረደባቸዉን ሁለት ስዊድናዊ ጋዜጠኞችን የአቶ መለስ መንግሰት እንዲለቅ ጠንካራ ዉይይት በማካሄድ ላይ እንዳለ ተገለፀ። “ባለፉት ጥቂት ቀናት ከኢትዮጵያ ባለስልጣኖች ጋር ስንነጋገር ነበር፡ ሁለቱ ጋዜጠኞች ሊፈቱ ይችላሉ የሚል ተስፋ አለን” በማለት ከጉዳዩ አሳሳቢነት የተነሳ ማንነታቸዉ እንዳይገለፅ የፈለጉ አንድ ከፍተኛ የአዉሮፓ ...

Read More »

በትግራይ መለስን እንደ ቁምነገረኛ የሚቆጥረውና ንግግሩን የሚሰማ ሰው እየቀነሰ መምጣቱ ተነገረ

የካቲት 8 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በትግራይ መለስ ዜናዊን እንደ ቁምነገረኛ የሚቆጥረውና ንግግሩን የሚሰማ ሰው እየቀነሰ መምጣቱን አቶ አስራት አብረሀ ተናገሩ በተለያዩ ጽሁፋቸው የሚታወቁት የአረና ትግራይ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሆኑት አቶ አስራት አብረሀ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ  ፣ “ድሮ የመለስን ንግግር ለመስማት የትግራይ ሰው ይጓጓ ነበር፣ መለስ ንግግር ካደረገ በሁዋላም አድናቆቱን ይገልጥ ነበር፣ በቅርቡ መለስ በፓርላማ ያደረገውን ንግግር ብዙ የመቀሌ ...

Read More »

ባለፉት 20 ዓመታት ለደረሰው ጥፋት ዋነኛው ተጠያቂ መለስ ናቸው ተባለ

የካቲት 8 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-መለስ ሰሞኑን በፓርላማ ያቀረቡት ሪፖርት፤ መንግስታቸው መዳከሙን የሚያመለክት ነው ያሉት ሶስት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፤ባለፉት 20 ዓመታት ለደረሰው ጥፋት ዋነኛው ተጠያቂም ራሳቸው ናቸው ሲሉ ተናገሩ። በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ላይ ጠንካራ ትችት የሰነዘሩት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮቹ የመድረኩ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣የ አንድነቱ አቶ አስራት ጣሴ እና  የ የኢዴፓው አቶ ሙሼ ሰሙ ናቸው።  አቶ መለስ ዜናዊ ሰሞኑን  የበጀት ...

Read More »

የአረብ ሳት ስርጭቶች የሚታወኩት ከኢትዮጵያ በሚለቀቅ ሞገድ ነው ተባለ

የካቲት 8 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የሊባኖስ የኮምንኬሽን ሚኒስትር የሆኑት ኒኮላስ ሽናዊ  የአርብሳት ከፍተኛ ባለስልጣኖችን ጠቅሰው ለዘ ደይሊ ስታር ለተባለው የሊባኖስ ጋዜጣ እንደተናገሩት በአረብሳት የሚተላለፉት ስርጭቶች እየታወኩ ያሉት የኢትዮጵያ መንግስት ስርጭቱን ለማፈን በሚያደርገው ሙከራ መሆኑን የአረብሳት ባለስልጣናት ለኢትዮጵያ መንግስት የጻፉትን ደብዳቤ አይተው አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት አረብሳትን ለማፈን እንዳስገደደው ሚኒሰትሩ ገልጠዋል። የሊቢያ እና የግብጽ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ ...

Read More »

በደባርቅ ወረዳ የሚገኙ መምህራን የጀመሩት አድማ ዛሬ ማብቃቱ ተመለከተ

የካቲት 7 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የደሞዝ ጭማሪ እና የተለያዩ የመብትና አስተዳደራዊ ጥያቄዎችን በማንሳት ከትናንት ጀምሮ በየትምህርት ቤቶች ግቢ ውስጥ ተቃውሞዎችን ሲያደርጉ  የነበሩት መምህራን፣ በዛሬው እለት አድማቸውን ያቋረጡት ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ከወላጆችና ተማሪዎች ጋር በተደረገ ውይዒት መሰረት ነው።  የወረዳው ባለስልጣናት መምህራኑ ካደረጉት ህገወጥ የስራ ማቆም አድማ የፖለቲካ እጅ እንዳለበት ቢናገሩም፣ ይህን አይነቱን ፍረጃ የተቃወሙ አንዳንድ መምህራን ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸው ታውቋል። ...

Read More »

መንግስት የቀድሞ ሰራዊት አባላትን እና በጡረታ የተገለሉ የኢህአዴግ ተቀናሽ ሰራዊትን ለመመለስ ውይይቶችን እያካሄደ መሆኑ ታወቀ

የካቲት 7 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-መንግስት የቀድሞ ሰራዊት አባላትን እና በጡረታ የተገለሉ የኢህአዴግ ተቀናሽ ሰራዊት አባላትን ወደ መከላከያ ለመመለስ ሰሞኑን በተለያዩ አካባቢዎች ውይይቶችን እያካሄደ መሆኑ ታወቀ በሰሜን ሸዋ ዞን 167 ተቀናሽ የሰራዊት አባላት ሰሞኑን በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት ተስብስበው እንደነበር የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የተቀናሽ ሰራዊት አባላት ወደ መከላከያ እንዲመለሱ ከደብር ዘይት አየር ሀይል አባላት የተውጣጡ መኮንኖች ለማሳመን ጥረት ቢያደርጉም ፣ ...

Read More »

“የብአዴን አባል ካልሆንክ መቀደስ አትችልም ተብዬ ተባረርኩ” ሲሉ አንድ ካህን ተናገሩ

የካቲት 7 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-“የኢህአዴግ- ብአዴን አባል ካልሆንክ፤በቤተ-ክርስቲያን ውስጥ መቀደስ አትችልም ተብዬ ተባረርኩ”ሲሉ አንድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ካህን ተናገሩ።  በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በኖኖ ወረዳ ማሩ ጉቴ በሚባል ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ሲኖሩ የነበሩት ቀሲስ ገረመው ናደው ተሰማ፤ ለፍኖተ-ነፃነት እንደተናገሩት ከገዥው ፓርቲ በኩል የቀረበላቸውን የፖለቲካ ፓርቲ አባልነት ጥያቄ አልቀበልም በማለታቸው፤ከቤተ-ክርስቲያን አገልግሎታቸው ከመታገዳቸውም በላይ  በሚደርስባቸው የተለያዬ በደል  ካለፉት ...

Read More »