Amsterdam

በአማሮ ወረዳ 3 የ መከላከያ ሰራዊት አባላት በታጣቂዎች ተገደሉ

በአማሮ ወረዳ 3 የ መከላከያ ሰራዊት አባላት በታጣቂዎች ተገደሉ ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) የአካባቢው ነዋሪዎች በሰራዊቱ አባላት ላይ ጥቃት የፈጸሙት የኦነግ ታጣቂዎች ናቸው ቢሉም፣ በመንግስት በኩል እስካሁን የተሰጠ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የለም። የግድያው መንስዔ ላለፉት 16 ወራት የዘለቀው በአማሮ ወረዳ የሚካሄደው በጉጂና በኮሬ ማህበረሰቦች መካከል ያለው ግጭት እንደገና በማገርሸቱ ነው። ባለፈው አርብ በስራ ላይ በነበሩ ...

Read More »

የቀደሞው የመረጃና ደህንነት ሰራተኛ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠባቸው።

የቀደሞው የመረጃና ደህንነት ሰራተኛ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠባቸው። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ለጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ በተዘጋጀው የድጋፍና የምስጋና ሰልፍ ወቅት የተፈጸመውን የሽብር ድርጊት አቀነባብረዋል ተብለው ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር በዋሉት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠ። ባለፈው ቀጠሮ አቶ ተስፋዬ ...

Read More »

የዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች ተገቢውን ትምህርት ማግኘት ባለመቻላቸው ትምህርታቸውን አቋረጡ።

የዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች ተገቢውን ትምህርት ማግኘት ባለመቻላቸው ትምህርታቸውን አቋረጡ። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) በዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች በተቋሙ አስተዳደር ለሚደርስባቸው አስተዳደራዊ በደሎች መፍትሄ እንዲሰጣቸው በተደጋጋሚ ጊዜያት ቢጠይቁም ምላሽ ማግኘት አልቻሉም። ይህን ተከትሎ ትምህርታቸውን በተገቢው ሁኔታ መከታተል ባለመቻላቸው ለማቋረጥ መገደዳቸውንና አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጠን ሲሉ ለጤና ጥበቃ ሚንስቴር በደብዳቤ አሳውቀዋል። የመማር ማስተማሩ አስመልክቶ በጻፉት ደብዳቤ ላይ ...

Read More »

ወደ ስድስት መቶ የሚሆኑ ሶማሊያውያን የተገደሉበት አንደኛ ዓመት ሢታሰብ ተከሳሹ በአደባባይ እንዲወገድ ተደረገ። በአዲስ አበባና በሶማሊያ ከአርባ ዓመት በኋላ በረራ የተጀመረ ሲሆን፣ በዕለቱ አልሸባብ ጥቃት ፈጽሟል። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) በሶማሊያ ታሪክ አሰቃቂውን የቦምብ ፍንዳታ በመፈጸም ስድስት መቶ ለሚጠጉ ሰላማውያን ዜጎች ሞት ምክንያት የሆነው ሀሰን አዳን ይስሀቅ ትናንት የሟቾቹ አንደኛ ዓመት ሲከበር በአደባባይ እንዲወገድ ተደርጓል። ...

Read More »

በአጋሮ ከተማ በተነሳ ተቃውሞ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ

በአጋሮ ከተማ በተነሳ ተቃውሞ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም ) ዛሬ አርብ የከተማው ከንቲባ አቶ ናዚሙ ሁሴን፣ የጎማ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ራይስ እንዲሁም የድርጅት ቢሮ ሃላፊው አቶ ነዚህ ሙሃመድ አሚን እንዲወርዱ ለመጠየቅ በተሰባሰቡ ነዋሪዎች ላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በወሰዱት እርምጃ በሞተስ ሳይክል ሲጓዝ የነበረ አንድ ሰው በጥይት ተመትቶ ህይወቱ አልፏል። በከተማዋ የንግድ ቤቶች ...

Read More »

በቡራዩ ነጋዴዎች የንብረት ካሳ አለማግኘታቸውንና ስራም አለመጀመራቸውን ገለጹ

በቡራዩ ነጋዴዎች የንብረት ካሳ አለማግኘታቸውንና ስራም አለመጀመራቸውን ገለጹ ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም )ባለሆቴሎቹ ለኢሳት ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ለደረሰው የንብረት ውድመት የከተማው መስተዳድር የወደመውን ንብረት ምዝገባ እና ግምት ቢያካሂድም እስካሁን ወደስራ እንዲመለሱ ለማድረግ ይህ ነው የሚባል ተግባር አላከናወነም፡፡ የቡራዩ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሃላፊ በበኩላቸው የወደመውን ንብረት የመመዝገቡ ስራ በቀጣዩ ሳምንት እንደሚጠናቀቅ ገልፀዋል፡፡ ለተፈናቃዮቹ ማቋቋሚያም ሆነ ለደረሰው የንብረት ...

Read More »

በራያ ህዝብ ላይ የሚደርሱት የመብት ጥሰቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። አሁንም 23 ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ናቸው።

በራያ ህዝብ ላይ የሚደርሱት የመብት ጥሰቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። አሁንም 23 ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ናቸው። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም )ካለ ሕዝብ ፈቃድ ከወሎ ክፍለሃገር ተወስዶ ወደ ትግራይ እንዲካለሉ የተደረጉት ራያዎች በተደጋጋሚ ጊዜያት የሚያነሱትን የማንነት ጥያቄዎች ለማዳፈን በትግራይ ክልል የሚደርስባቸው መጠነ ሰፊ የመብት ጥሰቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በአዲሱ ዓመት የትምህርት ዘመን ህገ መንግስቱ የሰጠን መብት ይከበርልን፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋችን ...

Read More »

አርበኞች ግንቦት7 በሃረር ከተማ ስብሰባ እንዳያካሂድ ተከለከለ

አርበኞች ግንቦት7 በሃረር ከተማ ስብሰባ እንዳያካሂድ ተከለከለ ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም )ክልሉ ለድርጅቱ መስከረም 18 ቀን 2011 ዓም በጻፈው ደብዳቤ “ በጸጥታ ምክር ቤት ጉዳዩ ታይቶ በክልሉ ባለው ሃገራዊ ሁኔታ አንጻር ተገምግሞ የተጠየቀው ፍቃድ አለመፈቀዱን እንገልጻለን” ብሎአል። ክልከላውን በማስመልከት ልክልሉ ም/ል ፕሬዚዳንት አቶ ጋቢሳ ተስፋዬና ለጸጥታ ክፍል ሃላፊው አቶ አበበ መብራቱ ስልክ በተደጋጋሚ ብንደውልም ሊመልሱልን አልቻሉም። ...

Read More »

በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አረፉ

በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አረፉ ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም ) ነዋሪነታቸው በደቡብ አፍሪካ ጆበርግ ከተማ ውስጥ የበረው አንጋፋው አገር ወዳድ ሼህ ወርቁ ኑሩ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ በደቡብ አፍሪካ ስደተኞች ተወዳጅና አሰባሳቢ አባት ...

Read More »

ኦነግ በምዕራብ ወለጋ የመንግስት ታጣቂዎችን ትጥቅ እያስፈታ ከመሆኑም በላይ ያገታቸው ነጋዴዎች መኖራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ።

ኦነግ በምዕራብ ወለጋ የመንግስት ታጣቂዎችን ትጥቅ እያስፈታ ከመሆኑም በላይ ያገታቸው ነጋዴዎች መኖራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 01 ቀን 2011 ዓ/ም ) ማንነታቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት “በኡላ ኖሌ” ወረዳ የኦነግ ታጣቂዎች መንግስት ያስታጠቃቸውን የአካባቢ ሚሊሺያዎችን ትጥቅ በማስፈታት የጦር መሳሪያዎችን ወስደዋል። የኦነግ ታጣቂዎች በዚሁ ወረዳ ጌጡ ገበየሁ የሚባል ታዋቂ ነጋዴን አፍነው የወሰዱ ሲሆን፤ ነጋዴው እስካሁን የደረሰበት አልታወቀም። ከኖሌ ...

Read More »