በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አረፉ

በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አረፉ
( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም ) ነዋሪነታቸው በደቡብ አፍሪካ ጆበርግ ከተማ ውስጥ የበረው አንጋፋው አገር ወዳድ ሼህ ወርቁ ኑሩ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ በደቡብ አፍሪካ ስደተኞች ተወዳጅና አሰባሳቢ አባት ነበሩ።
በኢትዮጵያ የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የሰብዓዊ መብት መጣስን፣ የህወሃት/ኢህአዴግ አፈና በዜጎች ላይ ሲያደርስ የነበረውን ሰቆቃ በማውገዝ የዜጎች መብት እንዲከበር ሳይሰለቹ ድምጻቸው ከሚያሰሙት የሃይማኖት አባቶች መሃከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። የኢሳት ዝግጅት ክፍል ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እንገልጻለን።