በአባቶች መሀከል የሚካሄደው እርቅ በቀጣዩ ወር ይቀጥላል ተባለ

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ የተጀመረው የቀዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ባጸደቃቸው አጀንዳዎች ላይ ውይይቱን ቅጥሏል።የእርቁ ሂደት በቀጣዩ ወር እንዲቀጥለም ወስኗል።ሰኞ ዕለት የተጀመረው የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ከቀረጻቸው አጀንዳዎች የፓትሪያሊክ መርጫ ህግ ማውጣት አንዱ መሆኑ ተመልክቷል፤ደጀሰላም እንደዘገበው ከፍተኛ የገንዘብ ብክለት የተመዘገበባቸው የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሰራ አስኪያጅ ንብረእድ ኤልያስ አብርሃ ከሃላፊነታቸው የመነሳታቸው ጉዳይ እያበቃለት ...

Read More »

በጄኔራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ በገርባ ህዝብ ላይ የተፈጸመውን ግድያ አወገዘ

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ኦነግ “የህወሀት ሽብር ለእውነተኛ ዲሞክራሲ የሚደረገውን  ትግል አይገታውም” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለአለፉት 11 ወራት መንግስት በሀይማኖታችን ጣልቃ አይግባብን በማለት ተቃውሞ ሲያሰሙ መቆየታቸውን አስታውሷል። ሙስሊሞች ያቀረቡት ጥያቄ፣ የይስሙላው ህገመንግስት እንኳን የሚፈቅደው ነው የሚለው ኦነግ፣ ሰሞኑን በገርባ ህዝብ ላይ የተፈጸመው ግድያ ፣ ሌላው የህወሀት ጭካኔ  ማሳያ ነው ብሎአል። አዲሱ የይስሙላ ጠቅላይ ...

Read More »

ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ሽልመቷን ተቀበለች

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሽብርተኝነት ተከሳ በቃሊቲ እስር ቤት የምትገኘው ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ የ2012 የ ዓለማቀፍ የሴቶች ሚዲያ ፍውንዴሽን ሽልማትን ተቀበለች።   የኢትዮፎረሙ ዳዊት ከበደ እንደዘገበው  የጋዜጠኛ ርዕዮትን ሽልማት ኒዮርክ በተካሄደው ዝግጅት ላይ ተገኝቶ  የተቀበለው የፀሀይ አሳታሚ ድርጅት ባለቤት ጋዘተጠኛ ኤልያስ ወንድሙ ነው። ——————– ሽልማቱን ለመቀበል ቀደም ሲል የታጨው ጓደኛዋ ስለሺ ሃጎስ ቢሆንም፤ ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ...

Read More »

ጤና ጥበቃ ከታራሚዎች 62 በመቶዎቹ በአዕምሮ ጭንቀት በሽታ የሚሰቃዩ ናቸው አለ

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰሞኑን ብሔራዊ የአዕምሮ ጤና ስትራቴጂን ይፋ ባደረገበት ወቅት በለቀቀው መረጃ፤ በአዲስ አበባ፣ በቃሊቲና በተለያዩ ማረሚያ ቤቶች ከሚገኙት ታራሚዎች መካከል 61 ነጥብ 9 በመቶ የሚሆኑት በከፍተኛ የአዕምሮ ጭንቀት የተጠቁ መሆናቸውን ያመለክታል። ታራሚዎቹን ለአዕምሮ ጭንቀት ከሚዳርጓቸው ምክንያቶች መካከል በጠባብ ክፍል ውስጥ መታፈግ፣ በግዳጅ ለብቻ እንዲገለሉ ማድረግ ፣ብዙም እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ በቀጣይ ህይወት ...

Read More »

ካታርና ኢትዮጵያ የዲፕሎማቲክ ግንኙነት ሊጀምሩ ነው

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ላለፉት አራት አመታት የዲፕሎማቲክ ግንኙነታቸውን አቋርጠው የነበሩት ኢትዮጵያና ካታር ግንኙነታቸውን እንደገና ለመጀመር ማቀዳቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል። ኢትዮጵያ ከአራት አመታት በፊት ካታር በኢትዮጵያ ውስጥ አፍራሽ ስራዎችን እየሰራች ነው በሚል የዲፐሎማሲ ግንኙነቷን መቋረጧ ይታወሳል። ኢትዮጵያ ካታር በሱማሊያ የእስልምና አክራሪ ሀይሎችን ትደግፋለች የሚል ተደጋጋሚ ቅሬታ ስታቀርብ ቆይታለች። የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆኑት ...

Read More »

ኢትዮጵያ ከአምናዋ ሻምፒዮን ዛምቢያ ጋር ተመደበች

ጥቅምት ፲፬ (አስራ ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በመጪው ጥር በደቡብ አፍሪካ የሚካሄደው የ29ኛው እግር ኳስ ዋንጫ የምድብ ድልድል ወጥቷል፤ ኢትዮጵያ በምድብ ሶስት፤ ከአምናዋ ቻምፒዮን ዛምቢያ፤ ቡርኪናፋሶና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላለች። ዛሬ፤ ረቡእ ጥቅምት 14 ቀን በደቡብ አፍሪካዋ ከተማ ደርባን የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማና የአፍሪካ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት፤ ኢሳ አያቱ በተገኙበት ስነስርአት በወጣው እጣ፤ ኢትዮጵያ ከሶስቱ አገሮች ጋር ተደልድላለች። ደቡብ አፍሪካ በምድብ ...

Read More »

በኦጋዴን በመንግስት ወታደሮችና በኦብነግ መካከል ውጊያ ተቀስቀሷል

ጥቅምት ፲፬ (አስራ ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በኬኒያ ናይሮቢ ሲካሄድ የነበረው ድርድር መቆረጡን ተከትሎ በኢትዮጵያ ኦጋዴን አካባቢ ውጊያ መቀጠሉን ኦብነግ አስታወቀ:: የኦብነግ የኢትዮጵያ ሀላፊ  አቶ ሀሰን አብዱላሂ ለኢሳት በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮች ላይ ጥቃት በመሰንዘር ጉራት ማድረሳቸውን አመልክቶል:: በሶማሌ ክልል ወደ ደግሀቡር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የኢትዮጵያ መንግስት ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ላይ ኦብነግ በሰነዘረው ጥቃት በርካታ ወታደሮች መገደላቸው ተመልክቶል:: ግድያውን ተከትሎ በአካባቢው ...

Read More »

በጋምቤላ የከፍተኛ ፍ/ቤት ዳኞችና ባለስልጣናት ተባረሩ

ጥቅምት ፲፬ (አስራ ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የጋምቤላ ክልል ምክርቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የከፍተኛ ፍ/ቤት ዳኞችን ጨምሮ ባላስልጣናትን እንዳባረረ ገለጠ:: የአኞዋክ ሬዲዮ ሪፖርተር አጉዋ ጊሎ ከኢሳት ሬዲዮ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ እንደገለጠው የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛና ምክትላቸው እንዲሁም የጤና ቢሮ ሀላፊና የደህንነት ሰራተኛ አቶ  ኦቻላ ከስልጣንና ከሀላፊነታቸው ከተባረሩት ውስጥ ይገኙበታል:: የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች የተባረሩት በጋምቤላ ከሚገኙ ታጣቂ ሀይሎች ጋር ...

Read More »

ኦህዴድ በአራት ቡድኖች ተከፍሎ እየተጨቃጨቀ መሆኑን ፍኖተ ነጻነት ዘገበ

ጥቅምት ፲፬ (አስራ ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ)፤ በአራት ቡድኖች ተከፍሎ በታላቅ ሽኩቻ ውስጥ ይገኛል ተባለ። ፍኖተ ነጻነት ታማኝ ምንጮችን ጠቅሶ በድረ ገጹ እንዳሰፈረው፤ በአቶ ኩማ ደመቅሳ የሚመራው “ኦህዴድ-መለስ” የሚባለው አንጃ ከህወሀት ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያለው ሲሆን፤ የአቶ መለስን ራእይ እውን ከማድረግ ውጪ የተለየ አመለካከቶችን ሁሉ የሚቃወም ነው። አቶ ኩማ ደመቅሳ፤ አቶ ሙክታር ከድር፤ ወ/ሮ ...

Read More »

በተባበሩት አረብ ኤሚሬት በአሰሪዋ ከፎቅ የተወረወረችው ሴት ስቃይዋ እየተባባሰ ነው

ጥቅምት ፲፬ (አስራ ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በተባበሩት አረብ ኤሚሬት አቡዳቢ፤ በአሰሪዋ ከፎቅ የተወረወረችው የ20 አመት ኢትዮጵያዊ እግር ላይ በደረሰው ጉዳት በአልጋ መቅረቷ ተነገረ። በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ቆንስላ የወጣቷን ፓስፖርት ወስዶም እንዳትንቀሳቀስ አግዷታል። ወጣቷ በአቡዳቢ ፍርድ ቤት የተወሰነላትን 500 ሺህ ድርሀም የጉዳት ካሳ ክፍያ ማግኘት አልቻለችም። ወጣት መዲና መሀመድ ከአመት በፊት አቡዳቢ ገብታ እራሷንና ቤተሰቧን ሰው ቤት በመስራት ለመርዳት የወጠነችውን ...

Read More »