ወ/ሮ አዜብ አቶ መለስን ለመተካት እየታገሉ ነው

ነሀሴ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለቤታቸውን በሞት ካጡ በኃላ በእሳቸው እግር ተተክተው የህወሃትን የሊቀመንበርነት ቦታ ተቆናጥጦ ወደ ኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበርነት ለመሳብ ድጋፍ የማሰባሰብ ዘመቻ ላይ መክረማቸውን ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡ በኢህአዴግ 36 የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውስጥ ብቸኛ ሴት ሆነው በመስከረም ወር 2003 ዓ.ም ከፍተኛውን የፓርቲ ሥልጣን በባለቤታቸው በአቶ መለስ ዜናዊ ልዩ ድጋፍ ማግኘት የቻሉት ወ/ሮ አዜብ ...

Read More »

በጀርመን የሚገኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ማህበር ካህናት አቡነ መርቆርዮስ ወደ መንበራቸው እንዲመለሱ ጠየቁ

ነሀሴ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ማህበሩ ነሀሴ 26 ቀን 2004 ዓም በጀርመን አገር ፍራንከፈርት ከተማ ባወጣው መገልጫ ላይ ” እስካሁን ቤተ ክርስቲአኑዋን ለሁለት የከፈለው ጉዳይ በእግዚአብሄር ፈቃድ አንደኛው አባት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል ስለዚህ አሁን በህይወት ያሉት ቀድሞም ያለአግባብ በመንግስት ሀይል ከስልጣናቸው እንዲወገዱ የተደረጉት አባት ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ወደ መንበራቸው ሊመለሱ ይገባል። ማህበሩ ያለፈው ስህተት እንዳይደገም ...

Read More »

አቶ ሀይለማርያም ግልገል ጊቤ ሦስት በታሰበው ጊዜ አይጠናቀቅም አሉ

ነሀሴ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በቀጣዮቹ ዓመታት የሀይል እጥረት ያጋጥማል የሚል ከፍተኛ ሥጋት አለ ከአንድ ዓመት በሁዋላ ይጠናቀቃል ተብሎ እቅድ የተያዘለት የግልገል ጊቤ  ሀይል ማመንጫ ግንባታ በተባለው ጊዜ እንደማይጠናቀቅ  አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ አስታወቁ። በመስከረም 2006 ዓ.ም. ይጠናቀቃል ተብሎ ዕቅድ የተያዘለት የግልገል ጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫ ግንባታ በወቅቱ እንደማይጠናቀቅ በመረጋገጡ፣ ሊያጋጥም የሚችለውን የኃይል እጥረት ለመቅረፍ ያስችላል የተባለ አዲስ ...

Read More »

የአቶ መለስን ዜና እረፍት ሲሰሙ አላዘኑም ወይም አላግጠዋል የተባሉ ወደ ሰንዳፋና ሸዋ ሮቢት እስርቤቶች ተላኩ

ነሀሴ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር አንድ የመነጋገሪያ አጀንዳ የሆነው የአቶ መለስ ዜናዊ የቀብር ስነስርአት በርካታ አስገራሚ ነገሮችን እያሳየ በመጠናቀቅ ላይ ነው። እሁድ እለት አብያተ ቤተክርስቲያናት ለአቶ መለስ ልዩ የጸሎት ስነስርአት እንዲያዘጋጁ መታዘዙ በተሰማ ማግስት፣ በተለያዩ ዝግጅቶች ላይ አላግጣችሁዋል ወይም በደንብ አላዘናችሁም የተባሉ ከተለያዩ አካባቢዎች የተሰባሰቡ በርካታ ወጣቶች በሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ (ማዕከላዊ)፣ ሰንዳፋ እና ...

Read More »

የአንድነት ፓርቲ ልሳን የሆነው ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ እንዳይታተም ታገደ

ነሀሴ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ሀሙስ እለት ተጨማሪ ልዩ ህትመታቸውን በብርሀንና ሰላም ማተሚያ ቤት ለማሳተም የ18 እሺ ጋዜጣ ዋጋ ለመክፈል የሄዱት የአንድነት ፓርቲ ልሳን የሆነው ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ አዘጋጆች በማተሚያ ቤቱ ሁለተኛ ለእናንተ ጋዜጣ ህትመት በእኛ ማተሚያ ቤት አይታተምም ብለው እንደከለከሉዋቸው ታውቋል። የጋዜጣው ዝግጅት ክፍል ባልደረቦች የማተሚያ ቤቱን ሀላፊዎች ያነጋገሩ ሲሆን፣ ፣ እናንተ የጠቅላይ ሚኒሰትሩን ሞት ...

Read More »

የአፋር ፎረም ኮንፈረንስ በመካሄድ ላይ ነው

ነሀሴ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በቤልጂየም ብራሰልስ ጉባኤያቸውን የሚያካሂዱት የለያዩ የአፋር ተወላጆችና ድርጅቶች የተሰባሰቡበትን ዝግጅት የአስተባበሩት አቶ ጋዝ አህመድ ለኢሳት እንደገለጡት ከ፣ ጅቡቲ፣ ከኢትዮጵያ፣ ካናዳ፣ አውሮፓ እና ከሌሎችም አካባቢዎች የተውጣጡ ከ አንድ መቶ አምሳ በላይ ሰዎች ተገኝተው መግለጫ ሰጥተዋል። የአውሮፓ ፓርላመንት ምክትል ሀላፊና የተለያዩ የአውሮፓ ህብረት ባለስልጣናት እንዲሁም በኢትዮጵያ ላይ በርካታ መጽሀፍትን የጻፉት ታዋቂው ምሁር ፕሮፌሰር ...

Read More »

የኢህአዴግ ካድሬዎች ህዝቡ ፍቅሩን ከግለሰብ ወደ ድርጅት እንዲለውጥ ጥረት እንዲያደርጉ ታዘዙ::

ነሀሴ ፳፬ (ሀያ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ሰሞኑን በመካሄድ ላይ ያለው አቶ መለስ ዜናዊን ልዩ ሰው አድርጎ የመሳል እንቅስቃሴ ድርጅቱን ስጋት ላይ እየጣለው በመምጣቱ ካድሬዎች የፕሮጋንዳ ስራቸውን ከግለሰብ ወደ ድርጅት እንዲያዞሩ ታዘዋል። ኢህአዴግ በመጀመሪያ በአቶ መለስ ዜናዊ የግለሰብ ስብእና አስታኮ ስልጣኑን ለማደላደል የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ቀይሶ የነበረ ቢሆንም፣ የፕሮፓጋንዳው እንቅስቃሴ አቅጣጫውን እየቀየረ መምጣቱ ድርጅቱን ስጋት ላይ ጥሎታል። አቶ መለስ ...

Read More »

ህዝቡ በአቶ መለስ ዜናዊ የተንዛዛ የለቅሶ ስርአት ተቃውሞውን እየገለጠ ነው::

ነሀሴ ፳፬ (ሀያ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የኢሳት ዘጋቢዎች ያነጋገሩዋቸው የህብረተስብ ክፍሎች እንደገለጡት የአቶ መለስ ዜናዊ የተንዛዛ የለቅሶ ስርአት በህይወታቸው ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያመጣ ነው። አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ በኢግዚቢሽን ማእከል ውስጥ በሚካሄደው ባዛር  ባለፈው ሳምንት በ20 ሺ ብር የንግድ ቦታ የገዛ ሰው ለኢሳት እንደተናገረው ፣ የአቶ መለስ ዜናዊን እረፍት ተከትሎ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ሆነ የራዲዮ ጣቢያዎች ማስታወቂያዎችን ማስተላለፍ ...

Read More »

አዲስ አበባ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በከፍተኛ የጸጥታ ቁጥጥር ስር ትገኛለች ተባለ::

ነሀሴ ፳፬ (ሀያ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ዘጋቢያችን እንደገለጠው በዛሬው እለት እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌደራል ፖሊስ አባላት በከተማዋ የተለያዩ ክፍሎች ተሰማርተው የጸጥታ ስራ እየሰሩ ነው። የጸጥታ ቁጥጥሩ እንዲጠናከር የሆነበትን ትክክለኛ ምክንያት ለማወቅ ባይቻልም በአንድ በኩል የሙስሊሙ ማህበረሰብ በነገው እለት ተቃውመ ያነሳል በሚል ፍርሀት ወይም በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው የአቶ መለስ ዜናዊ ልዩ የሽኝት መርሀግብር እንዳይደናቀፍ ...

Read More »

የግብጹ መሪ በሶሪያ የሚካሄደውን የሰብአዊ መብት ጥሰት አወገዙ::

ነሀሴ ፳፬ (ሀያ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- አዲሱ የግብጽ መሪ፣ ሙሀመድ ሙርሲ በኢራን በሚካሄደው የገለልተኛ አገሮች ጉባኤ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት የሶሪያ ተቃዋሚዎች የሚያካሂዱትን ትግል መደገፍ የሞራል ግዴታ ነው ። የሶሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ዋሊድ ሙአለም የፕሬዚዳንት ሙርሲ ንግግር ” በሶሪያ የሚካሄደውን ደም ማፈሰስ ይበልጥ የሚያባብስ ነው” ብለዋል። 120 አባላት ባሉት በዚህ ጉባኤ ላይ ፕሬዚዳንት ሙርሲ ሲናገሩ ” ...

Read More »