ኢሕአዴግ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሪዎችን እየመለመ ነው

ግንቦት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ሪፖርተር እንደዘገበው ምልመላውን እያከናወኑ ያሉት የሥልጣን ዘመናቸው በቅርቡ የሚያበቃው ከንቲባ ኩማ ደመቅሳና ምክትላቸው አቶ አባተ ስጦታው፣ የአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ገብረ ፃድቃንና ምክትላቸው አቶ ጀማል ረዲ ናቸው፡፡ የትራንስፖርት ሚኒስትሩ  ድሪባ ኩማ፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩ  መኩሪያ ኃይሌ፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ  ሲራጅ ፈርጌሳ፣ የፌዴራል ፖሊስ ጄነራል ኮሚሽነር ወርቅነህ ገበየሁ፣ ወ/ሮ አዜብ ...

Read More »

በኖርዌይ ኦስሎና አካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቅዳሜ በ18.05.13 ህዝባዊ ውይይት አደረጉ።

ግንቦት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ውይይቱ በሀገራችን በግፍ ለተገደሉ፤ በእስር ለሚንገላቱና ለፍትህ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ለሚሰቃዩና ለተሰደዱ ወገኖች የህሊና ፀሎት በማድረግ ተጀምሯል። በርካታ ታዳሚዎችም ሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን ሰልፍ በመደገፍ ጥቁር ልብስ ለብሰው ተገኝተዋል። ውይይቱ የተጠራው በኖርዌይ ለወገን ደራሽ ግብረ ሀይል ሲሆን. በውጪ ሀገር የሚኖረው ኢትዮጵያዊ በኢትዮጵያ  ፖለቲካ ውስጥ ስለሚጫወተው ሚናና በሀገር ቤት በሰማያዊ ፓርቲ ስለተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ፣. ...

Read More »

ባህርዳር የተፈጸመው ግድያ እንቆቅልሽ እስካሁን አልተፈታም

ግንቦት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በባህርዳር 17 ሰዎችን በጥይት አርከፍክፎ በግፍ ከገደለው የፌደራል ፖሊስ አባል ፈቃዱ ናሻ ጋር በተያያዘ ግድያው ሲፈጸም በዝምታ ተመልክታችሁዋል በሚል 10 የፊድራል ፖሊስ አባላት ታሰረዋል፡፡  የገዳዩ የቀድሞ ፍቅረኛም ድርጊቱ ከተፈጸመበት ቀን አንስቶ በህግ ቁጥጥር ስር እንደምትገኝ ታውቋል፡፡ የፊደራል ፖሊስ ዋና  አዛዥ ጄኔራል ወርቅነህ ገበየሁ ትላንት የተጎጅ ቤተሰቦችን ጎብኝተዋል፡፡ የተጎጅ ቤተሰቦች ለጄኔራል ወርቅነህ ገበየሁ “ገዳዩ ...

Read More »

ታዋቂ አፍሪካውያን ወደ ውጭ ተዘርፎ በሚወጣው ገንዘብ ላይ የቡድን 8 እና 20 አገራት እርምጃ እንዲወስዱ ግፊት ማድረግ ጀመሩ

ግንቦት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ግሎባል ፋይናንሻል ኢንቴግሪቲ ለኢሳት በላከው መረጃ የቀድሞው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ ኮፊ አናን፣ የታዋቂው የነጻነት አባት የኔልሰን ማንዴላ ባለቤት ግራሺያ ሚሼል እና ሌሎች ታዋቂ አፍሪካውያን በጋራ ለቡድን 8 እና ለቡድን 20 አገራት መሪዎች በጻፉት ደብዳቤ ከአፍሪካ ባለፉት 9 አመታት ተዘርፎ በውጭ ባንኮች የተቀመጠው 385 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወደ አህጉሪቱ እንደሚለስ ጠይቀዋል። ኮፊ ...

Read More »

የደቡብ ሱዳን ዜጎች የኢትዮጵያ ጦር ከሱዳን እንዲወጣ ጠየቁ

ግንቦት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ደቡብ ሱዳናውያን ጥያቄ እያቀረቡ የሚገኙት የኢትዮጵያ ጦር ዜጎቻችን በሰሜን ሱዳኖች ሲገደሉ በቂ መከላከል አላደረገም በማለት ነው። እንደ ፊረንጆች አቆጣጠር  ሜይ 4፣ 2013 አብየ ውስጥ የአካባቢ የጎሳ ገዚ የነበረው ሚስተር ኲኦል ዴንግ ኲኦል በመሲርያ ጎሳ አባላት በኢትዬጲያ ሰላም አስከባሪ ፊት መገደሉ ይታወሳል። በወቅቱ በተደረገው የተኩስ ልውውጥም ኢትዮጵያውያን ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ተገድለዋል። ግድያው የኢትዬጵያ ሰላም ...

Read More »

ከ300 በላይ መኪኖች በጉሙሩክ ተይዘው ለ 2 አመታት ያለስራ መቀመጣቸው ተዘገበ

ግንቦት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-አዲስ አድማስ እንደዘገበው   አስጐብኚ ድርጅቶች፣ የገቢዎችና የጉምሩክ ባለስልጣን ሃላፊዎች አቤቱታችንን ለመስማትም ሆነ እኛን ለማነጋገር ፍቃደኛ ባለመሆናቸው እንግልት ደርሶብናል ሲሉ ባካሄዱት ስብሰባ ገልጸዋል። በመቶ የሚቆጠሩ ድርጅቶች በአባልነት የያዘው የአስጐብኚዎች ማህበር ትናንት በጠራው አስቸኳይ ስብሰባ፣ የፀረ ሙስና ኮሚሽን እንቅስቃሴን እንደሚደግፍ በመግለፅ፣ የኛ አቤቱታና መረጃ ለኮሚሽኑ ጠቃሚ ግብአት ይሆናል ብሏል፡፡ የማህበሩ አባላት የሆኑ አስጐብኚ ድርጅቶች ከባለስልጣኑ ...

Read More »

አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በአምስት ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸናፊ ሆነች

ግንቦት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ዛሬ ሻንጋይ ቻይና ላይ በተደረገው የዳይመንድ ሊግ ውድድር፣ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በአምስት ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር 14፡ደቂቃ ከ45ነጥብ 92 ሰከንድ በሆነ ሠዓት በመግባት አሸናፊ ሆነች። በዚሁ ውድድር እንደምታሸንፍ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቷት የነበረችው የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ ባለድል የሆነችው ታዋቂዋ አትሌት መሰረት ደፋር 14ደ ቂቃ፡47 ነጥብ 76 ሰከንድ በሆነ ሰዓት 2ኛ ሆና ስታጠናቅቅ፣ ኬንያዊቷ ...

Read More »

ከአፋር ጋድሌ ጋር በተያያዘ ባለስልጣናትን እና ፖሊሶችን ጨምሮ 14 ሰዎች ታሰሩ

ግንቦት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ባለፈው ሳምንት ከአፋር ጋድሌ ወታደራዊ ንቅናቄ ጋር በተያያዘ  14 ሰዎች መታሰራቸውን፣ ከታሰሩት መካከልም፣ የቀበሌው ሊቀመንበር፣ የወረዳ ምክር ቤት አባል፣ አንድ ፖሊስ እና ሽማግሌዎች እንደሚገኙበት ለማወቅ ተችሎአል። አብዛኞቹ የተያዙት በፌደራል ፖሊሶች ሲሆን በቅርቡ 70 የሚሆኑ የአፋር ወጣቶች አፋር ጋድሌ የሚባለውን  የትጥቅ ትግል በማድረግ ላይ የሚገኘውን ድርጅቶች መቀላቀላቸውን ተከትሎ ነው። ከታሰሩት መካከል የሩማይቶ ቀበሌ ሊቀመንበር ...

Read More »

አቶ መላኩ ፈንታ በአንድ ትንሽ ክፍል ውስጥ ብቻቸውን መታሰራቸውን ተናገሩ

ግንቦት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከሙስና ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙት የየኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር    አቶ መላኩ ፋንታ በእስር ቤት ውስጥ ልብቻቸው በአንድ ትንሽ ክፍል ውስጥ ከመታሰራቸውም በላይ ለአንድ ቀን ብቻ ለ10 ደቂቃ እንዲናፈሱ እንደተፈቀደላቸው ተናግረዋል። ቀኑን ሙሉ በትንሽ ክፍል ውስጥ ተዘግቶብኝ ነው የምውለው ያሉት አቶ መላኩ ፣ መንግስት ለሚያውቀው በሽታቸው የሚሆን መድሀኒትም ቢሆን ከጊዜ በሁዋላ ...

Read More »

በቤይሩት በቤት ሰራኝነት ተቀጥራ የምታገለግል አንዲት ኢትዮጵያዊ ወጣት፣ አሰሪዋን ሆን ብላ በፈላ ውሃና በእሳት አቃጥላለች በሚል በቁጥጥር ስር መዋሏን ደይሊ ስታር የተሰኘው ድረ ገጽ ዘገበ።

ግንቦት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በዚሁ የዜና ዘገባ መሰረት በሰሜን ቤይሩት ግዛት ማስቲታ ጀቢል በተሰኘ ስፍራ የምትኖረው የ70 ዓመቷ አረጋዊት ወ/ሮ ሳሚያ፣ ድንቅነሽ የተሰኘች የ24 ዓመት ዕድሜ ያላት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛዋ፣ ከነሃስ በተሰራ ቅርፃ ቅርጽ ጭንቅላቷን ከመታቻት በኋላ የፈላ ውሃ ፊቷ ላይና ደረቷ ላይ በማፍሰስ ጉዳት አድርሳባታለች። አደጋ የደረሰባት ግለሰብ ለህክምና በአቅራቢያው ወደሚገኝ ሆስፒታል እንደተወሰደች የሚያትተው ይኸው ዘገባ፣ ...

Read More »