የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ በናጀሪያዊው ስደተኛ ላይ ያደረሱት ጥቃት ቁጣን ቀሰቀሰ

ማጋቢት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኬፕታውን የሚገኙ ፖሊሶች በአንድ ናይጀሪያዊ ስደተኛ ላይ ያደረሱት ጥቃት በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን ከተለቀቀ በሁዋላ የአለም ህዝብ ቁጣውን እየገለጸ ነው። የደቡብ አፍሪካዊ ፖሊስ ድረጊቱን የፈጸሙ ሁለት ፖሊሶች መታሰራቸውን ቢገልጽም የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች ግን የደቡብ አፍሪካ ፖሊሶች በተለይም በስደተኞች ላይ የሚያደርሱት እንግልት ለከት እያጣ መጥቷል ይላሉ። የደቡብ አፍሪካ ፖሊሶች ከውጭ አገር ስደተኖች ገንዘብ እንደሚቀበሉ፣ ...

Read More »

በሀረር ከተማ የተነሳውን የእሳት ቃጠሎ ተከትሎ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ነዋሪዎች በፖሊሶች ተበተኑ

ማጋቢት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለምዶ ሸዋ በር መብራት ሃይል ግቢ እየተባለ በሚጠራው የንግድ ማእከል ላይ ምክንያቱ በውል ባልታወቀ ሁኔታ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በብዙ መቶወች የሚቆጠሩ ነጋዴዎችን ንብረት አውድመዋል። ነጋዴዎች እንደሚሉት እሳቱ ሆን ተብሎ በመስተዳድሩ ባለስልጣናት እንዲነሳ የተደረገ ነው። ነጋዴዎቹ አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ በተደጋጋሚኦ ሲጠየቁ እንደነበር እንዲሁም የእሳት አደጋ መኪኖች ዘግይተው እሳቱን ለማጥፋት መምጣታቸው ቃጠሎው በመስተዳድሩ ሰዎች ...

Read More »

አንድነት ፓርቲ 2ኛውን ዙር የሚሊዮኖችን እንቅስቃሴ በተለያዩ ከተሞች ሊጀምር ነው

ማጋቢት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ለሦስት ወራት በሚካሄደው ክፍል ሁለት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ሪፎርም” በሚለው ዘመቻ፣ በዋነኛነት በተመረጡ 14 ከተሞች እና በሦስት ተጓዳኝ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ ይካሄዳል። የመሬትን አጀንዳ የሁለተኛው ዙር የመታገያ አጀንዳ ለምን እንዳደረገ ፓርቲው ሲያብራራ፣ “በባለሃብት ስም ገበሬው ከይዞታው መፈናቀሉ፤ በከተሞች በልማት ስም ዜጎች እየተፈናቀሉ ለጎዳና ላይ ኑሮ መዳረጋቸው፤ ሰብአዊና ...

Read More »

15 የቅማንት ብሄረሰብ አባላት መታሰራቸውን 14ቱ ደግሞ የደረሱበት አለመታወቁ ተገለጸ

ማጋቢት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን በጭልጋ፣ በአርማጭሆና በመተማ ወረዳዎች እና በአካባቢው ያሉ የቅማንት ብሔረሰብ አባላት እያቀረቡ ያለውን  የማንነትና ህገመንግስታዊ ጥያቄ ለማፈን ሰሞኑን በድምሩ 29 ያህል የቅማንት ተወላጆች መታሰራቸውንና መታፈናቸውን የቅማንት ብሔረሰብ የማንነት ጥያቄና ራስ አስተዳደር ይፈቀድልኝ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡ ኮምቴው ከየካቲት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ጅምሮ በአዲስ መልክ የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጆች ላይ ...

Read More »

በሚሊዮን ብር የሚቆጠር የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን ዘርፈዋል የተባሉ ተከሰሱ

ማጋቢት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሪፖርተር እንደዘገበው ከኢትዮጵያ መድኃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ግምታቸው ከ3.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በመስረቅ ወንጀል የተጠረጠሩ አዲስ በላይ እና ተባባሪዎቹ ሁሴን ከድር ፣ ማኒና ተስፋ ማርያም እና ታደሰ ባቲ ክስ ተመስርቶባቸዋል። ሰባት ዓይነት የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን የሰሌዳ ቁጥሩ አ.አ 3-37987 በሆነ አይሱዙ መኪና ጭነው ሊሰወሩ ሲሉ እንደተደረሰባቸው የፌዴራል የሥነ ...

Read More »

የቁጫ ወረዳ የአገር ሽማግሌዎች “ለ16ኛ ጊዜ ጠ/ሚንስቴር ጽ/ቤት አቤት ብንልም የሚሰማን አጣን” አሉ

የካቲት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን በቁጫ ወረዳ ከማንነትና ከመልካም አስተዳደር ጋር ተያይዞ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ በአካባቢው ያለው አፈና እንዲቀንስ ፣ በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎች እንዲፈቱ እንዲሁም ከቀያቸውና ከስራቸው የተፈናቀሉት ዜጎች ወደ ቦታቸውና ወደ ስራቸው እንዲመለሱ ለመጠየቅ ትናንት ወደ አዲስ አበባ በማምራት ለጠ/ሚኒስቴር ጽ/ቤትና በፌደሬሽን ምክር ቤት ለ16ኛ ጊዜ አቤቴታቸውን ያቀረቡ የአገር ሽማግሌዎች ...

Read More »

የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት በየረር ባሪ ጎሳ አባላት ላይ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል የምክር ቤት ድጋፍ አገኙ

የካቲት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት የሆኑት አብዲ ሞሀመድ ኦማር ከማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ  በጎሳው አባላት የተነሳውን ተቃውሞ በሃይል ለመጨፍለቅ የሶማሊ ክልል አዲሱ ምክር ቤት ድጋፍ እንደሰጣቸው ታውቋል። ከክልሉ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው አቶ አብዲ የየረር ጎሳ አባላትን አልሸባብ እየተባለ ከሚጠራው የሶማሊያ ታጣቂ ሃይል ጋር ግንኙነት እንዳላቸው አድርገው በማቅረብ ምክር ቤቱ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ፈቃድ ...

Read More »

የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ለሶስት አዳዲስ የንግድ የኤፍኤም ራዲዮ ፈቃድ ለመስጠት የሚያስችለውን ጨረታ አወጣ፡፡

የካቲት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ጨረታው ለይስሙላ የወጣ መሆኑንና የሚሰጣቸው ሰዎች አስቀድመው የተዘጋጁ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ባለስልጣኑ አስካሁን ራዲዮ ፋናን ጨምሮ ለአራት ያህል የንግድ ኤፍኤም ጣቢዎች ፈቃድ የሰጠ ሲሆን የረጅም ሞገድ ራዲዮ ጣቢያ እና የግል ቴሌቭዥን ጣቢያ ፈቃድ መስጠት በአዋጅ ቁጥር 533/1999 ስልጣን የተሰጠው ቢሆንም እስካሁን ተግባራዊ ለማድረግ ፈቃደኝነት ሳይታይበት ቀርቶአል፡፡ ባለስልጣኑ ባለፉት ...

Read More »

ሳውድ አረቢያና ሌሎች የባህረ ሰላጤው ሃገራት ከግብጽ ጎን መቆማቸው ታወቀ

የካቲት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞውን የግብጽ ፕሬዚዳንት ሙሃመድ ሙርሲን በመደገፍና በእርሳቸው ላይ የተወሰደውን እርምጃ በመቃወም ጠንካራ አቋም የያዘችውን ካታርን በዲፕሎማሲ ዘመቻ ለማግለል ሳውድ አረቢያና ሌሎች የባህረ-ሰላጤው አገራት ዲፕሎማቶቻቸውን ከአገሪቱ አስወጥተዋል። አዲሱ የግብጽ መንግስት የካታር ልኡካኑን ያስወጣ ሲሆን፣ ይህን ተከትሎም ሳውድ አረቢያ፣ ባህሬንና ዩናይት አረብ ኤምሬትስ ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል። የግብጽ የፖለቲካ አካሄድ የአረብ አገራትን እየከፋፈለ ነው። ...

Read More »

አሜሪካ እና ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ የተራራቀ አቋም መያዛቸውን ፑቲን ተናገሩ

የካቲት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሩሲያው መሪ ቭላድሜር ፑቲን ከአሜሪካው አቻቸው ባራክ ኦባማ ጋር ለ2 ሰአታት ከተወያዩ በሁዋላ ሁለቱ አገሮች በዩክሬን ላይ ያላቸው አቋም የተራራቀ መሆኑን ገልጸዋል። አሜሪካ፣  ሩሲያ የአለምን ህግ መጣሱዋን በመግለጽ ከዩክሬን ግዛት እንደትወጣና ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትመለስ ስትሻ፣ ሩሲያ በበኩሉዋ በዩክሬን የሚኖሩ ዜጎቼን ከጥቃት የመከላከል መብት አለኝ በማለት ህግ አለመጣሱዋን ትናገራለች። ክሪሚያ የምትባለው ...

Read More »