የአቶ አንዳርጋቸውን መያዝና ተላልፎ መሰጠት ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ቁጣቸውን እየገለጹ ነው

ሰኔ ፳፯(ሃያ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንዲት እናት ” እኔ ሁለት ልጆች አሉኝ፣  ልጆቼን ዛሬ ብሰጥ ደስ ይለኛል” ሲሉ በአቶ አንዳርጋቸው መያዝ የተሰማቸውን ስሜት በለቅሶ ገልጸዋል። አንድ ወጣት ደግሞ እርሱና ጓደኞቹ በአቶ አንዳርጋቸው መያዝ ወደ ትግል ፈጥነው እንዲገቡ እንደሚያደርጋቸው ገልጸዋል። “ቀድሞ ዘርዘሩን ዘርቷል” በሚል ቅኔ የተቀኙት አንድ ኢትዮጵያ ደግሞ በአንዳርጋቸው መስዋትነት፣ ነጻነታችንን እውን እናደርጋለን ብለዋል ሌላ ወጣት ደግሞ ” ...

Read More »

ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ዛሬም የተቃውሞ ድምጻቸውን ሲያሰሙ ዋሉ።

ሰኔ ፳፯(ሃያ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአንዋር መስጊድ እጅግ በርካታ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በተካሄደው ተቃውሞ ፣ መንግስት “መጅሊሱን ለህዘበ ሙስሊሙ እንዲያስረክብ እንዲሁም የታሰሩትን መሪዎች እንዲፈታ” ጠይቀዋል። “ትግሉ የጽኑዎች ነው፣ ፍትህ ይስፈን፣ የእምነት ቤቶቻችን ይከበሩ፣ የታሰሩት ይፈቱ፣ የትግላችንን መነሻ እናሳካው የማነፍርበት የትግል መዳረሻችን ነው፣ አፈና ግፍና ማስገደድ ይቁም” የሚሉ መፈክሮች ተሰምተዋል። ሙስሊሙ ኢትዮጵያውያን በረመዳን ጾም መግቢያ ጀምሮ ጠንካራ ተቃውሞዎችን እየሰማ ...

Read More »

በሸኮና መዠንገር በተነሳው ግጭት አንድ የልዩ ሃይል አዣዝ ተገድሏል።

ሰኔ ፳፯(ሃያ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በርካታ የሌሎች አካባቢ ሰዎች ተፈናቅለው፣ በቴፒ ከተማ ኤግዢቢሽን አዳራሽ ሰፍረዋል። ሰፋሪዎች በምግብ እና በውሃ ችግር ለአደጋ መጋለጣቸው ታውቋል። እስካሁን ከ700 ያላነሱ ሰዎች ተፈናቅለዋል። ግጭቱ ካለፉት 3 ቀናት ጀምሮ ከቁጥጥር ውጭ መውጣቱ ተነግሯል። ልዩ ፖሊስና የወረዳው ፖሊስ፣ ዘመናዊ መሳሪያ ከታጠቁት የሸኮና መዠንገር ተዋጊዎች ጋር እየተዋጋ መሆኑ ታውቋል። ሸኮና መዠንገር መሬታቸው ጻኑ ቀበሌ ለደቡብ ክልል ...

Read More »

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል አንዳርጋቸው በአስቸኳይ እንዲለቀቅ አስጠነቀቀ

ሰኔ ፳፮(ሃያ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል ” አንዳርጋቸው የማይጨበጥ ጽኑ መንፈስ እንጂ አንድ ግለሰብ አይደለም” በሚል ርእስ ባወጣው ጠንካራ መግለጫ ” የየመን መንግሥት የፈጸመው ድርጊት እጅግ  ስህተት  መሆኑን  ዘግይቶም ቢሆን  ተረድቶ የነፃነት ታጋዩን እንዲለቅ” አስጠንቅቋል።  ይህ ባይሆን ግን ይላል የግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል ” አንዳርጋቸው ወያኔ እጅ ውስጥ ከገባ  የትውልዱ  የበቀል ሰይፍ ከዛሬ ጀምሮ ከሰገባው መውጣቱን እንዲያውቁት ...

Read More »

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የጸጥታ ሃይሎች መታገታቸውን ተከትሎ የሚሰጡት አስተያየቶች ቀጥለዋል

ሰኔ ፳፮(ሃያ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመላ አገሪቱ የስልክ መልእክቶችን በመደወል ለአቶ አንዳርጋቸው ጀግንነት ድጋፋቸውን የሚገልጹ፣ በእርሱ መታሰር የኢትዮጵያ ህዝብ የተሰማውን ስሜት የሚገልጹና ስለቀጣዩ ህዝባዊ እርምጃ አስተያየቶችን የሚሰጡ በርካታ የስልክ መልእክቶች ለኢሳት እየደረሱ ነው። “እድሜየ 50ዎቹ አጋማሽ ነው፣ ከስራ ውየ ስገባ የሰማሁት ዜና አስደንግጦኛል፣ ስሜቴን መቆጣጠርም አልቻልኩም፣ ቤተሰቤን ልጆቼን ትቼ ትግሉን ለመቀላቀል ወስኛለሁ” በማለት የተናገሩት አንድ የመንግስት ሰራተኛ፣ የመን ...

Read More »

የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች በአቶ አንዳርጋቸው መታገት ዙሪያ መግለጫ እያወጡ ነው

ሰኔ ፳፮(ሃያ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአፓ የየመን የጸጥታ ሃይሎች በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የወሰዱትን እርምጃ በጽኑ አውግዞ፣ የአገሪቱ መንግስት በአስቸኳይ እንዲለቀው ጠይቋል። አንዳርጋቸው በአምባገነኖች ፍርድ ቤት በሽብር ወንጀል ተከሶ ሞት የተፈረደበት በመሆኑ፣ ተላልፎ ቢሰጥ ለከፋ ስቃይና ሞት ሊዳረግ እንደሚችል አስጠንቅቋል። የአቶ አንዳርጋቸው መታሰር አደገኛ የሆነ አሰራር የሚፈጥር በመሆኑ ድርጊቱ በጽኑ ሊኮነን ይገባዋል ሲል ኢህአፓ አሳስቧል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ተነስቶ ...

Read More »

በመላው አለም የሽብር ጥቃቶች ሊፈጸሙ ይችላል በሚል ጥበቃዎች ተጠናክረዋል

ሰኔ ፳፮(ሃያ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአሜሪካ መንግስት ባወጣው መግለጫ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያላቸው የሽብር ድርጅቶች ጥቃት ለመፈጸም በመዘጋጀት ላይ ለመሆናቸው አስተማማኝ መረጃ እንደደረሰው አመልክቷል። ይህን ተከትሎም በእንግሊዝ፣ በአሜሪካ እና በሌሎችም አገራት አየር መንገዶች ላይ የሚታየው ጥበቃ ተጠናክሯል”” ኡጋንዳም በአየር መንገዷ ላይ ሽብር ሊፈጸም ይችላል በሚል ከፍተኛ ጥበቃ እያደረገች ነው።

Read More »

የአቶ አንዳርጋቸው  እገታ ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ከየአቅጣጫው ቁጣቸውን እየገለጹ ነው

ሰኔ ፳፭(ሃያ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየመን መንግስት የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን  ማገቱን ተከትሎ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚኖሩ ዜጎች ቁጣቸውን እየገለጹ ነው። አላማጣ አካባቢ የሚኖሩ አንድ አስተያየት ሰጪ  ” የየመን መንግስት ያገተው አንዳርጋቸውን ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ነው። በዚህ የቁርጥ ቀን ልጅ ላይ አንድ ነገር ቢደረግ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆ ብሎ ይነሳል። የመን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ...

Read More »

በእስራኤል እና በፍልስጤሞች መካከል ያለው ውጥረት እንደጨመረ ነው

ሰኔ ፳፭(ሃያ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንድ ታፍኖ የተወሰደ የፍልስጤም  ወጣት መገደሉን ተከትሎ ፍልስጤማውያን ቁጣቸውን እየገለጹ ነው። የ17 አመቱ ወጣት ሙሃመድ አቡ ካድር በመኪና ታፍኖ ሲወሰድ የአይን ምስክሮች ማየታቸውን ተናግረዋል።  ፍልስጤማውያን ከእስራኤል ፖሊሶች ጋር መጋጨታቸውን ተከትሎ የእስራኤሉ መሪ ቤንጃሚን ናታንያሁ  ግድያውን አውግዘው፣ የእየሩሳሌም ከንቲባ የህዝቡን ቁጣ እንዲያበርዱ አሳስበዋል። የፍልስጤም መሪዎች በበኩላቸው እስራኤል 3 ወጣቶች መገደላቸውን ተከትሎ የወሰደችው የበቀል እርምጃ ...

Read More »

ግንቦት7 አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለማስፈታት ጥረቱን መቀጠሉን አስታወቀ

ሰኔ ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የንቅናቄው የስራ አስፈጻሚ አባልና የህዝባዊ እምቢተኝነት ዘርፍ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ አበበ ቦጋለ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፣ የየመን የጸጥታ ሃይሎች አቶ አንዳርጋቸውን በአስቸኳይ ይለቁት ዘንድ ለአገሪቱ ፕሬዚዳንት ደብዳቤ ከመጻፍ ጀምሮ በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፎችን እና ሌሎች እንቅስቃሴዎችን የሚያደርጉበትን መንገድ እያመቻቹ ነው። ግንቦት7 ለየመን ፕሬዚዳንት ፊልድ ማርሻል አብዱ ራቡ ማንሱር ሃዲ እኤአ ሰኔ ...

Read More »