ቱርክ በአገሯ ያለውን የሳውዲን ኢምባሲ መረመረች

ቱርክ በአገሯ ያለውን የሳውዲን ኢምባሲ መረመረች ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 06 ቀን 2011 ዓ/ም ) በሳውዳረቢያዊው ዜጋ ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ ግድያ ዙሪያ የሚደረገውን ምርመራ አጠናክራ የቀጠለችው ቱርክ በአገሯ ባለው የሳውዲ ኢምባሲ በመግባት ምርመራ ማካሄዷ ታውቋል። ኢስታንቡል የሚገኘው ቆንስላ ተወካይ የሆኑት ሙሃመድ አል ኦታይቢ በግል አውሮፕላን ከአገሪቱ መውጣታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። በሳውዲ ንጉሳዊ ቤተሰብ ላይ ከፍተኛ ትችት በማቅረብ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ካሾጊ፣ ከቀድሞ ...

Read More »

በአማሮ ወረዳ 3 የ መከላከያ ሰራዊት አባላት በታጣቂዎች ተገደሉ

በአማሮ ወረዳ 3 የ መከላከያ ሰራዊት አባላት በታጣቂዎች ተገደሉ ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) የአካባቢው ነዋሪዎች በሰራዊቱ አባላት ላይ ጥቃት የፈጸሙት የኦነግ ታጣቂዎች ናቸው ቢሉም፣ በመንግስት በኩል እስካሁን የተሰጠ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የለም። የግድያው መንስዔ ላለፉት 16 ወራት የዘለቀው በአማሮ ወረዳ የሚካሄደው በጉጂና በኮሬ ማህበረሰቦች መካከል ያለው ግጭት እንደገና በማገርሸቱ ነው። ባለፈው አርብ በስራ ላይ በነበሩ ...

Read More »

የቀደሞው የመረጃና ደህንነት ሰራተኛ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠባቸው።

የቀደሞው የመረጃና ደህንነት ሰራተኛ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠባቸው። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ለጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ በተዘጋጀው የድጋፍና የምስጋና ሰልፍ ወቅት የተፈጸመውን የሽብር ድርጊት አቀነባብረዋል ተብለው ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር በዋሉት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠ። ባለፈው ቀጠሮ አቶ ተስፋዬ ...

Read More »

የዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች ተገቢውን ትምህርት ማግኘት ባለመቻላቸው ትምህርታቸውን አቋረጡ።

የዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች ተገቢውን ትምህርት ማግኘት ባለመቻላቸው ትምህርታቸውን አቋረጡ። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) በዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች በተቋሙ አስተዳደር ለሚደርስባቸው አስተዳደራዊ በደሎች መፍትሄ እንዲሰጣቸው በተደጋጋሚ ጊዜያት ቢጠይቁም ምላሽ ማግኘት አልቻሉም። ይህን ተከትሎ ትምህርታቸውን በተገቢው ሁኔታ መከታተል ባለመቻላቸው ለማቋረጥ መገደዳቸውንና አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጠን ሲሉ ለጤና ጥበቃ ሚንስቴር በደብዳቤ አሳውቀዋል። የመማር ማስተማሩ አስመልክቶ በጻፉት ደብዳቤ ላይ ...

Read More »

ወደ ስድስት መቶ የሚሆኑ ሶማሊያውያን የተገደሉበት አንደኛ ዓመት ሢታሰብ ተከሳሹ በአደባባይ እንዲወገድ ተደረገ። በአዲስ አበባና በሶማሊያ ከአርባ ዓመት በኋላ በረራ የተጀመረ ሲሆን፣ በዕለቱ አልሸባብ ጥቃት ፈጽሟል። ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) በሶማሊያ ታሪክ አሰቃቂውን የቦምብ ፍንዳታ በመፈጸም ስድስት መቶ ለሚጠጉ ሰላማውያን ዜጎች ሞት ምክንያት የሆነው ሀሰን አዳን ይስሀቅ ትናንት የሟቾቹ አንደኛ ዓመት ሲከበር በአደባባይ እንዲወገድ ተደርጓል። ...

Read More »

በአቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ፖሊስ የሚያደርገውን ምርመራ እንዲያጠናቅቅ ተጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 5/2011)የሰኔ 16ቱን የቦምብ ጥቃት አስተባብረዋል በሚል ወንጀል የተጠረጠሩት የብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ባልደረባ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ፖሊስ የሚያደርገውን ምርመራ እንዲያጠናቅቅ ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ ቀጠሮ ሰጠ ፡፡ ፖሊስ ችሎቱ በፈቀደለት 10 ቀናት የሰው ምስክር መቀበሉን ብሎም ከመስሪያ ቤታቸው የተገኘው ቦምብ ለምርመራ መወሰዱንና ሌሎች ተግባራትን ማከናወኑን ጠቅሷል፡፡ ፖሊስ የቀድሞው የደህንነት ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ኡርጌን በተመለከተ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ...

Read More »

የኤርትራው ፕሬዝዳንት ወደ አስመራ ተመለሱ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 5/2011)የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ያደረጉትን የሁለት ቀናት ጉብኝት አጠናቀው ዛሬ ወደ አስመራ ተመለሱ። ወደ አዲስ አበባ ያደረጉት ጉዞ በሁለቱ ሃገራት የሰላም ስምምነት ላይ ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ እንጂ በአንዳንድ ወገኖች እንደሚባለው ከኦነግ ጋር ለማሸማገል አይደለም ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ለኢሳት ገልጸዋል። ቅዳሜ ማለዳ አዲስ አበባ የገቡት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቄ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ግብዣ ወደ ...

Read More »

ብርጋዴር ጄኔራል ሃይሉ ጎንፋ ተሾሙ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 5/2011) ብርጋዴር ጄኔራል ሃይሉ ጎንፋ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ። በሳምንቱ መጨረሻ ብርጋዴር ጄኔራል ከማል ገልቹና ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ የኦሮሚያና የአማራ ክልሎች የጸጥታ ከፍተኛ ሃላፊዎች ሆነው መሾማቸው ይታወሳል። በምርጫ 1997 በኢትዮጵያውያን ላይ የተካሄደውን ጭፍጨፋ በመቃወምና፣የምርጫውን መጭበርበር በማውገዝ ሰራዊት ይዘው ወደ ኤርትራ የገቡት ብርጋዴር ጄኔራል ከማል ገልቹ የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደርና ጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ ሆነው በሳምንቱ መጨረሻ መሾማቸው ...

Read More »

ሰራዊቱ ያሉበትን ችግሮች ለመቅረፍ የማሻሻያ ርምጃዎች በመውሰድ ላይ ናቸው

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 5/2011)የኢትዮጵያ ሰራዊት ያሉበትን ችግሮች ለመቅረፍ በየደረጃው የማሻሻያ ርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆናቸውን ጄኔራል ሰአረ መኮንን ገለጹ። ወደ ቤተመንግስት የተጓዙትን የሰራዊቱን አባላት ድርጊት ጋጠወትና ጸረ ሕገ መንግስት በማለት የጠቀሱት ጄኔራል ሰአረ መኮንን ከድርጊቱ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ አመራሮቹ መታሰራቸውን ገልጸዋል። አስተማሪ የሆነ ርምጃ እንደሚወስድም ቃል ገብተዋል። ባለፈው ሳምንት ረቡዕ መስከረም 30/2011 ወደ ቤተመንግስት የተንቀሳቀሱት የአጋዚ ክፍለ ጦር አባላት መሆናቸውን የገለጹት ጄኔራል ...

Read More »

በሻሸመኔ አንድን ግለሰብን ዘቅዝቀው የሰቀሉ ለፍርድ ቀረቡ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 2/2011) በሻሸመኔ ከተማ ባለፈው ነሐሴ አንድን ግለሰብ ዘቅዝቀው በመስቀል የገደሉና በዕለቱ ብጥብጥ አስነስተዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች ለፍርድ መቅረባቸው ተገለጸ። ነሐሴ 6 ለኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ የልዑካን ቡድን በተዘጋጀው አቀባበል ላይ ግርግርና ሁከት በመፍጠር ግለሰቡን በአሰቃቂ ሁኔታ ግድለዋል ተብለው ከተጠረጠሩት 14 ግለሰቦች 6ቱ በትላንትናው ዕለት በምዕራብ አርሲ ዞን ከፍተኛው ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ለማወቅ ተችሏል። የሻሸመኔውን ሁከት ተከትሎ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ...

Read More »