ሙስሊሞች ወደ ሁዋላ መመለስ የለም አሉ

የካቲት 30 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በዛሬው የጁማ ሶላት ስግደት ላይ የተሰበሰቡ ከ300-400 ሺ የሚጠጉ ሙስሊሞች መንግስት ከእንግዲህ መሰብሰብ አትችሉም ቢላቸውም፣ እነርሱ ግን ወደ ሁዋላ እንደማይሉና በጥያቄያቸው እንደሚገፉበት ገልጠዋል። ዛሬ የኮሚቴው አባላት ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር ያደረጉትን ውይይት ለህዝቡ የፋ አድርገዋል። መንግስት ጥያቄዎችን በአግባቡ አለመመለሱንም እያንዳንዱ በአወልያ የተገኘው ሙስሊም ተረድቷል። መንግስት ከእንግዲህ ወዲያ በአወልያ መስጂድ የሚደረገው መሰባሰብ እንዳይቀጥል ፣ ቢቀጥል የኮሚቴው ...

Read More »

የአካል ጉዳተኞች የኤች አይ ቪ ኤድስ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዳልሆኑ ተገለፀ

የካቲት 30 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በኤች አይ ቪ ኤድስ ላይ የሚደረጉ ዘመቻዎችና ቅስቀሳዎችን ለማካሄድ በስራ ላይ የሚዉሉት የመገናኛ ስልቶች የአካል ጉዳተኞችን ግምት ዉስጥ ያላስገቡ በመሆናቸዉ በኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞች ለበሽታዉ ያላቸዉ ግንዛቤ ዝቅተኛ ከመሆኑም በላይ ከበሽታዉ ጋር የተያያዙ አግልግሎቶችን ሊያገኙ እንደማይችሉ አንድ የረድኤት ድርጅት የስራ ሃላፊ ገለፁ።  ሊያ ሰሎሞን በኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና ልማት ማእከል the Ethiopian Centre for Disability and ...

Read More »

ሼክ አላሙዲን በአፍሪካ አንደኛ ባለሀብት ተባሉ

የካቲት 30 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በኢትዮጵያ የሚገኙ የወርቅ ጉድጓዶችን እንዲሁም የነዳጅ ማውጫ ኩባንያ ባለቤት የሆኑት ሼክ አላሙዲን በአፍሪካ አንደኛ ባለሀብት ተባሉ የኢህአዴግ ደጋፊ የሆኑት ቢሊየነሩ ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን ይህን ማእረግ ያገኙት ናይጄሪያዊውን ቢሊየነር አሊኮ ዳጎቴን በመተካት ነው። የሼኩ አዲሱ የሀብት መጠን 12 ቢሊዮን 500 ሚሊየን ደርሷል። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ታላለቅ የንግድ ተቋማትን በርካሽ ዋጋ በመግዛት የሚወነጀሉት ሼክ አለሙዲን፣ ሚድሮክ ...

Read More »

የእህል ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ግራ ማጋባቱን ቀጥሎአል

የካቲት 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-አቶ መለስ ዜናዊ  በአ ገሪቱ የታየውን የገንዘብ ግሽበት ወደ አንድ አሀዝ እናወርዳለን ብለው በፓርላማ በተናገሩ በሳምንታት ውስጥ የምግብ ዋጋ በእጅጉ መጨመሩ ህዝቡን እያነጋገረ ነው። በአማራ ክልል ጤፍ እስከ 1400 ብር በመሸጥ ላይ መሆኑ  ህዝቡ በተለይም የመንግስት ሰራተኛው ምን እየሆነ ነው ማለት ጀምረዋል። የጤፍ መጨመር ሌሎች ምርቶችንም በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምሩ አድርጓል። የባህርዳር ዘጋቢያችን እንዳለው የአማራ ...

Read More »

በጋምቤላ አለመረጋጋቱ እንደቀጠለ ነው

የካቲት 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የጋምቤላው ዘጋቢያችን እንደገለጠው ሰሞኑን ኤለያ በሚባለው መስመር ታጣቂዎች የአንድ የግለሰብ እርሻን ሲጠብቁ በነበሩ ሶስት ዘበኞችና የእርሻው ባለቤት ላይ ጥቃት ከፍተው 3ቱ የአኝዋክ ተወላጅ የሆኑት ዘበኞች ወዲያው ሲገደሉ የእርሻው ባለቤት የሆኑት ሴት ባለሀብት ደግሞ በጸና ቆስለው ወደ አዲስ አበባ ተወስደው በመታከም ላይ ናቸው። ታጣቂዎች የሚሰነዝሩት ጥቃት እያየለ በመጣበት በአሁኑ ጊዜ የክልሉ ባለስልጣናትም ሆኑ የአላሙዲ ንብረት ...

Read More »

መንግስት ለሙስሊሙ ጥያቄ መልስ አለመስጠቱ ተቃውሞው እንዲቀጥል ያደርገዋል ተባለ

የካቲት 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ሙስሊሙ ማህበረሰብ ላቀረበው ጥያቄ መንግስት መልስ አለመስጠቱ ተቃውሞው እንዲቀጥል እንሚያደርገው አቶ አብዩ ያሲን ተናገሩ የሉቅማን ኢትዮጵያውያን ቤልጂየማውያን ሙስሊም ማህበር ሊቀመንበር የሆኑት አቶ አብየ ያሲን ለኢሳት እንደገለጡት መንግስት ሙስሊሙ ማህበረሰብ ላቀረባቸው 3 ጥያቄዎች ለአንዱም ተገቢውን መልስ አልሰጠም። “ተቃውሞው እንዳይካሄድ መንግስት አስጠንቅቋል  ከዚህ በሁዋላ የአወልያ ተቃውሞ የሚቀጥል ይመስልዎታል ለተባሉት ፣ አቶ አብዩ ተቃውሞው በመንግስት ያልተጀመረ በመሆኑ ...

Read More »

ስዊድናውያን ጋዜጠኞቹን በህገ-ወጥ መንገድ እንዲገቡ የላከው ተቋም ይከሰስ ተባለ

የካቲት 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:- “ስዊድናውያን ጋዜጠኞቹን ወደ አገራችን በህገ-ወጥ መንገድ እንዲገቡ የላከው ተቋም ቢከሰስ ፤በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ሊቀጣ ይችላል”ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና የኮሙኒኬሽን ዲን ተናገሩ። በህወሀት አባልነት የሚጠቀሱትና  በዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነትና የኮሙኒኬሽን ፋኩሊቲ ዲን የሆኑት  ዶክተር ገብረመድህን ስምዖን ይህን ያሉት፤በጉዳዩ ዙሪያ ለመንግስት ጋዜጠኞች በሰጡት አስተያዬት ነው። ስዊድናውያኑን ጋዜጠኞች ለማስፈታት እየተደረገ ያለው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት መፍትሔ ወደሚያገኝበት ደረጃ ላይ ...

Read More »

“ዛሬ መሣሪያ የሌለው ጦርነት ውስጥ ነን” ሲሉ ኢ/ር ኃይሉ ሻወል ገለጹ

የካቲት 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የመ ኢአድ አባል የሆኑ አንድ አባት፤ ታማ የሞተች ልጃቸውን እንዳይቀብሩ ተከለከሉ። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ ፕሬዝዳንት የሆኑት ኢ/ር ኃይሉ “ዛሬ መሳሪያ የሌለው ጦርነት ውስጥ ነን” ብለው የተናገሩት፤ 116ኛው የአድዋ ድል በዓል በፓርቲው ጽ/ቤት ሲከበር ነው፡፡   ከዛሬ 116 ዓመት በፊት ጣሊያን ንቆን መጥቶ ተዋርዶ መመለሱንና  አያቶቻችን፤ ጥቁር ህዝቦች ሁሉ የሚኮሩበትን ገድል  አድዋ  ላይበማስመዝገባቸውን ...

Read More »

ወንጂ ስኳር በርካታ ሰራተኞችን አባረረ

የካቲት 28 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ወንጂ ስኳር በርካታ ሰራተኞችን አባረረ የህወሀት ታጋዮች ከፍተኛ የአመራር ቦታዎችን ይዘዋል በአቶ አባይ ጸሀየ የሚመራው የስኳር ኮርፖሬሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ሰራተኞች እየተባረሩ ነው። እስካሁን ድረስ ከ300 በላይ ሰራተኞች ያለምንም ማስጠንቀቂያና ክፍያ እንዲሰናበቱ ተደርጓል። ሰራተኞቹ በሁለት ወራት ውስጥ ቤታቸውን እንዲያስረክቡ ሲጠየቁ፣ “ልጆቻችንን የት ልንበትኗቸው ነው፣ ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ ለምን ታስገድዱናላችሁ የሚል ተቃውሞ ...

Read More »

መንግስት ዘወትር አርብ የሚደረገው የተቃውሞ ስብሰባ እንዲቆም በጥብቅ አዘዘ

የካቲት 28 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአወሊያ በተሰባሰቡ ሙስሊሞች የተመረጡ 17 የኮሚቴ አባላት የካቲት 26 ቀን 2012 ዓም ከፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ሚኒስትሩ አቶ ሽፈራው ተክለማርያም በአወልያ እስከ ዛሬ ሲካሄድ የነበረው አይነት ተቃውሞ ከእንግዲህ ወዲያ እንዳይካሄድ፣ ቢካሄድ ሀላፊዎቹ ተጠያቂዎች እንደሚሆኑ አስጠንቅቀዋል። አቶ ሽፈራው የአወሊያ ተቃውሞ እንዲቆም ያዘዙት፣ ተቃውሞው ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ የሚንቀሳቀሱ ጸረ ሰላም ሀይሎች ሊጠቀሙበት መፈለጋቸውን መንግስት ...

Read More »