የአቶ መለስ ምስሎች አሁን ከአዲስአበባ ጎዳናዎች ላይ አልተነሱም

መጋቢት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-በአዲስአበባ እና በክልሎች የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ምስሎች በክብር እንዲወርዱ አቶ አዲሱ ለገሰ በመገናኛ ብዙሃን ያስተላለፉት ተማጽኖ እስካሁን ተግባራዊ አልሆነም። በቀድሞ የህወሃት ታጋይ ባለቤትነት የሚመራው ሪፖርተር ጋዜጣ የአቶ መለስ ምስሎች ጸሐይና ቁር እየተፈራረቀባቸው ስለሆነ በክብር ይነሱ ሲል መጻፉን ተከትሎ የመለስ ፋውንዴሽን መስራች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት የቀድሞ ምክትል ጠ/ሚኒስትር አቶ አዲሱ ለገሰ ፋውንዴሽኑን ...

Read More »

በፕሬስ የሚካሄድ ስም ማጥፋትን በተመለከተ የወንጀል ሕጉ ሊሻሸል ነው

መጋቢት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-በግለሰቦች እና ቡድኖች ላይ በፕሬስ የሚካሄዱ የስም ማጥፋትን ለመዳኘት የወንጀል ሕጉን ለማሻሻል መታቀዱ ተጠቆመ፡፡ ከ2005-2007 የሚቆየውና እስካሁን ሳይጸድቅ በውይይት ላይ የሚገኘው ብሔራዊ የሰብዓዊ መብት የድርጊት መርሃግብር ሰነድ ላይ እንደተመለከተው በመገኛኛ ብዙሃን አማካይነት የሚካሄዱና በተለይ በግለሰቦች እና ቡድኖች ላይ ያነጣጠሩ የሰም ማጥፋት ዘመቻዎችን ለማስቆም የወንጀል ሕጉን ለማሻሻል ጥናት ይካሄዳል፡፡ ይህው ሰነድ በመገናኛ ብዙሃን የሚቀርብ የስም ማጥፋት ...

Read More »

በኢትዮጵያ የትራፊክ አደጋዎችን ለመከላከል በሚል የምሽት ጉዞዎች ሊከለከሉ ነው

መጋቢት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-የትራንስፖርት እና መገናኛ ሚኒስቴር  የትራፊክ አደጋዎችን ለመቀነስ በምሽት የሚደረጉ  ጉዞዎችን ለማገድ ዝግጅት አጠናቅቄያለሁ አለ። እንደ ሚኒስቴር መስሪያ  ቤቱ ገለፃ ለመንገድ የትራፊክ ደህንነት አደጋ ዋነኛ መንስኤዎች ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር ፣ ከተፈቀደ የሰው ቁጥር በላይ መጫን ፣የመንገድ ህግና ስርአትን አለማክበር እና ህገ-ወጥ የሌሊት ጉዞ  ናቸው፡፡ ስለሆነም  በህገወጥ የሌሊት ጉዞ ተሳታፊ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን ለመቆጣጠር በሚኒስቴር መስሪያ ...

Read More »

ኢትዮ ቴልኮም ግንቦት7 ን መሰለሉ ተጋለጠ

መጋቢት ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-በህወሐት ጄኔራሎች አመራር ስር የወደቀው ኢትዮ ቴልኮም ፊን ሰፓይ በተባለ ሶፍትዌር የግንቦት 7 ለፍትህ፣ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ መረጃዎችን ሲሰልል መገኘቱን ተቀማጭነቱ አውሮፓ የሆነ አንድ አለማቀፍ የሶፍት ዌር ኩባንያ አጋልጧል። ሞርጋን ማርኩዊስ ቦሪ፣ ቢል ማርዛክ ፣ ክላውዲዮ ጋርኔሪ እና ጆን ስኮት ሬይላተን ሲትዝን ላብ በተባለ ዌብሳይት ላይ ባወጡት ጽሑፍ ፣ ፊን ስፓይ የግንቦት 7ትን መሪዎች ...

Read More »

ተመድ ሜጀር ጄነራል ዮሀንስ ገብረመስቀልን ለአቤይ ግዛት ሀላፊ አድርጎ ሾመ

መጋቢት ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ፣  ባንኪ ሙን ደቡብ እና ሰሜን ሱዳንን እያወዛገበ በሚገኘው የአቢይ ግዛት ለሰፈረው የሰላም አስከባሪ  ጦር ሜ/ጄኔራል ዮሀንስ ገብረመስቀልን ሾመዋል። ሜ/ጀኔራል ዮሀንስ ከዚህ ቀደም የሀይሉ አዛዥ የነበሩትን ሌተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን መተካታቸውን የተመድ ቃል አቀባይ ማርቲን ንስርኪይ ተናግረዋል። አዲሱ ሹም በወር ከ10 ሺ ዶላር በላይ እንደሚከፈላቸው ቀደም ብለን መዘገባችን ይታወሳል። ...

Read More »

ታሪካዊው ኢትዮጵያ ሆቴል ሊፈርስ ነው

መጋቢት ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያ ሆቴልን የገዙት ባለሀብት  ሆቴሉን ሙሉ በሙሉ አፍርሰው ሌላ ሆቴል ሊገነቡ እንደሆነ ተዘገበ። -ኢትዮጵያ ሆቴልና አዳማ ራስ ሆቴል ለባለሀብቱ የተሸጡት፤ በ134 ሚሊዮን ብር ነው በመሀል አዲስ አበባ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንግዶችን እንዲያስተናግድ ከ50 ዓመታት በፊት የተገነባው የኢትዮጵያ ሆቴል ፈርሶ፣ በምትኩ 60 ፎቅ ያለው ሆቴል እንዲገነባ የአዲስ አበባ አስተዳደር ካቢኔ መወሰኑን ምንጮቹን በመጥቀስ የዘገበው ...

Read More »

ለሙ እየተባለ በሚጠራው የአዲስ አበባ አካባቢ በተነሳ ግጭት በርካታ ሰዎች መሞታቸው ታወቀ

መጋቢት ፫(ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት ለሚ እየተባለ በሚጠራው ከአዲስ አበባ ወጣ ብሎ በሚገኝ አካባቢ በኮብል ድንጋይ ማንጠፍ ስራ ላይ በተሰማሩ የደቡብ እና የኦሮሞ ተወላጅ ሰራተኞች መካከል በተፈጠረ ግጭት ቁጥሩን በትክክል ለማወቅ ባይቻልም በርካታ ሰዎች ሙትና ቁስለኛ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሎአል።  ኢሳት ሰዎች መገደላቸውን መረጃ የደረሰው ቢሆንም፣ አሀዙን ከመንግስት ወይም ከሌላ ገለልተኛ ወገን ለማረጋገጥ አልቻለም። ይሁን እንጅ አንድ ...

Read More »

የአውሮፓ ህብረት የልኡካን ቡድን የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት አያያዝ ይገመግማል

  መጋቢት ፫(ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-30 አባላት ያሉት የአውሮፓ የሰብአዊ መብቶች የልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ እንደሚገመግም የዲፕሎማቲክ ምንጮች ገለጹ። የልኡካን ቡድኑ ዋና አላማ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ መገምገም ሲሆን፣ ከተለያዩ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች፣ በእስር ላይ ከሚገኙት ጋዜጠኞች እና የሲቪክና የሀይማኖት መሪዎች ጋር ይገናኛል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ በልማት ሽፋን የሚካሄደው  የልኡካን ቡድኑ ...

Read More »

አሰላ ትናንት በእሳት ዛሬ በመኪና አደጋ ተጠቃች

  መጋቢት ፫(ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በከተማዋ ትናንት ሌሊት 5 ሰአት ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ ከ10 በላይ ቤቶች የተቃጠሉ ሲሆን በብዙ ሚሊዮን የሚገመት ንብረትም ወድሟል። ኮምፒዩተር ቤቶች፣ ምግብ ቤቶች እና የሙዚቃ መሳሪያዎች መሸጫ ቤቶች በቃጠለው ከወደሙት መካከል ይገኙበታል። የከተማው ነዋሪዎች ፖሊሶች እና የመስተዳዳሩ ባለስልጣናት ከዝርፊያ ሊታደጉዋቸው እንዳልቻሉ ለኢሳት ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በዛሬው እለት አንድ ከባድ ተሽከርካሪ መኪና  መስመሩን ...

Read More »

የፍትህ ሚኒስቴር በስራ ላይ ያለውን የይቅርታ አዋጅ የሚያሻሽል አዲስ ረቂቅ ሕግ እያዘጋጀ መሆኑ ተሰማ፡፡

  መጋቢት ፫(ሶስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ሚንስቴሩ  ሕጉን ለማሻሻል የፈለገው እስር ቤቶች በእስረኞች ብዛት እየተጣበቡ በመምጣታቸው ነው ሲሉ ምንጮች ገልጸዋል። ከ1995 ዓ.ም ጀምሮ በፌዴራልና በክልሎች መንግስታት በሚገኙ እስር ቤቶች ቆይታቸው መልካም ስነምግባርን አሳይተዋል የተባሉ ከ62 ሺ በላይ እሰረኞች ይቅርታ ተደርጎላቸው ከእስር ቤት መውጣታቸው በአዲሱ ረቂቅ ሰነድ ውስጥ ተመልክቷል እስር ቤቶች በአመክሮ፣በይቅርታ ወይም ሙሉ የፍርድ ጊዜያቸውን ጨርሰው የሚለቀቁ እስረኞች ከእስር ...

Read More »