ትውልደ ኤርትራዊና ትውልደ ሶማሊያዊ የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት ሆነው ተመረጡ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በአሜሪካ በተካሄደው የአማካይ ዘመን ምርጫ ትውልደ ኤርትራዊና ትውልደ ሶማሊያዊ የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት ሆነው ተመረጡ። ለ435 የአሜሪካ ምክር ቤት ወንበር ትውልደ ሶማሊያዊዋ ኢላን ኦማር በአሜሪካ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሙስሊም የኮንግረስ አባልም ሆነዋል። የ34 አመቱ ዮሴፍ ንጉሴ በኤርትራ ውስጥ በሚካሄደው ጦርነት ሳቢያ ቤተሰቦቹ ወደ አሜሪካ ከተሰደዱ በኋላ በኮሎራዶ ግዛት መወለዱን በሕይወት ታሪኩ ላይ ተመልክቷል። ከኮሎራዶ ግዛት ለኮንግረስ ከተመረጡ አባላት አንዱ ...

Read More »

የኤርትራው ፕሬዝዳንት ወደ ጎንደር ከተማ ሊሄዱ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቄ የፊታችን አርብ ጎንደር ከተማ ይገባሉ ተባለ። ፕሬዝዳንቱ በአማራ ክልል በሚያደርጉት ጉብኝት የክልሉን ርዕሰ ከተማ ባህርዳርን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎችም ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተመልክቷል። ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የፊታችን አርብ ጎንደር ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የአማራ ክልል ባለስልጣናት አቀባበል እንደሚያደርጉላቸው ተመልክቷል። ኢትዮጵያና ኤርትራ ለ20 አመታት በጠላትነት የቆዩበት ምዕራፍ ባለፈው ሰኔ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የአስመራ ጉብኝት ፍጻሜ ...

Read More »

በሕገወጥ መንገድ የገቡ የጦር መሳሪያዎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011)ወደ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ በሶስት ወራት ውስጥ የገቡ የጦር መሳሪያዎች ብዛት ከ1 ሺ 500 በላይ መብለጡን ፖሊስ ገለጸ። የጦር መሳሪያዎቹም በአብዛኛው ቱርክ ሰራሾች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን በብዛት የሚገባውም በሱዳን በኩል እንደሆነ ተመልክቷል። በፌደራል ፖሊስ የተደራጁ ልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክተር ኮማንደር ከተማ ደባልቄ ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት እስከ መስከረም መጨረሻ ባሉት ሶስት ወራት 1 ሺ 560 ሕገ ወጥ ...

Read More »

በሕዝቦች ትግል የመጣው ለውጥ እንዳይቀለበስ መጠበቅ አለብን ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በሕዝቦች ትግል የመጣው ለውጥ እንዳይቀለበስ የተገኘውን ተስፋ፥ ነፃነት እና ሰላም መጠበቅ እንደሚያስፈልግ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገለጸ፡፡ ክልላዊ መንግስቱ በምዕራብ ጐንደር ዞን የተፈጠረውን ግጭት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ እንዳለው በነጋዴ ባህር አካባቢ ማንነታቸው ለጊዜው ያልታወቁ ግለሰቦች ባደረሱት ጥቃት የ4 ሰዎች ህይወት ሊያልፍ ችሏል፡፡ በዚህ መነሻ በተፈጠረ ግጭት በዞኑ መተማ እና ሽንፋ አካባቢዎች ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች ህይወትም መጥፋቱ ...

Read More »

ዓለም አቀፉ የቡና ቱሪዝም ፕሮግራም ተቃውሞ አስነሳ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) የቡና መገኛ ጂማ ነው በሚል በቡናና ሻይ ልማት ባለስልጣን የሚከበረው የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የቡና ቱሪዝም ፕሮግራም ተቃውሞ አስነሳ። ዛሬ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ህዝቡ አደባባይ በመውጣት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ አውግዟል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቡናና ሻይ ባለስልጣን ጋር በመተባባር የዘንድሮውን የቡና ቱሪዝም ለማክበር በከፋ የተያዘው ፕሮግራም ተሰርዞ በጂማ እንዲሆን መደረጉ ብሔርን ከብሔር የሚያጋጭና ታሪክን የሚቀማ ...

Read More »

በአፋር ተቃውሞ ሲደረግ ዋለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በአፋር የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲደረግ ዋለ። አሳይታ፣ አዳአር፣ በራሂሌ፣ ገላኢሉ፣ ዳሎል፣ ገዋኔና ኮነባ በተሰኙ የአፋር ከተሞች በተደረገው ተቃውሞ የክልሉን መንግስት የሚመራው ገዢ ፓርቲ ለህዝብ ስልጣኑን እንዲያስረክብ ተጠይቋል። ሁለተኛ ወሩን እያጠናቀቀ ያለው የአፋር ተቃውሞ ፌደራል መንግስቱ በአስቸኳይ ጣልቃ ገብቶ የክልሉ ህዝብ ከተደቀነበት አደጋ እንዲታደገው ጥሪ ቀርቧል። የአፋር ህዝብ ፓርቲ ለኢሳት እንደገለጸው የፌደራሉ መንግስት በቶሎ ምላሽ ካልሰጠ በአፋር ከፍተኛ ...

Read More »

በሊቢያ ኢትዮጵያውያን በስቃይ ላይ ናቸው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በሊቢያ ኢትዮጵያውያን በስቃይ ላይ መሆናቸው ተገለጸ። በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን ለቀናት ምግብና ውሃ አጥተው በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል። አብዛኞቹ ከጎንደር የተሰደዱ መሆናቸውን የሚገልጹት ኢትዮጵያውያኑ ባለፈው ቅዳሜ ገጀራና የጦር መሳሪያ የያዙ የሊቢያ ታጣቂዎች ድብደባ ፈጽመውባቸው ለከፍተኛ ጉዳት መዳረጋቸውን ተናግረዋል። ከእነዚህ ኢትዮጵያውያን መካከል የአምስት ቀን አራስ እናት እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል። ከኢትዮጵያውያኑ መካከል ...

Read More »

የቋሚ ኮሚቴዎች ቁጥር ወደ 10 ዝቅ ተደረገ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 27/2011) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያሉትን 20 ቋሚ ኮሚቴዎችና አንድ ልዩ ኮሚቴ በመሰብሰብ ወደ 10 ዝቅ ማድረጉን አስታወቀ። ለቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢነት ከተጠቆሙት አባላት ውስጥ ፓርላማው የሁለቱን ውድቅ ማድረጉም ተመልክቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ ሁለት ቋሚ ኮሚቴዎችን እንዲመሩ የተጠቆሙትን አቶ ሞቱማ መቃሳንና አቶ አማኑኤል አብርሃምን ውድቅ ያደረገበት ምክንያት ግን አልተገለጸም። የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩትና በቅርቡ ከዚህ ...

Read More »

አቶ ፍጹም አረጋ በአቶ ሽመልስ አብዲሳ ተተኩ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 26/2011) የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ በአቶ ሽመልስ አብዲሳ መተካታቸው ተገለጸ። አቶ ፍጹም አረጋ ለሌላ የስልጣን ቦታ መታጨታቸውንም ይፋ አድርገዋል። ከነገ ማክሰኞ ጥቅምት 27/2011 ጀምሮ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ሃላፊነትን ስራ የሚጀምሩት አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦዴፓ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል መሆናቸውም ተመልክቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡበት ግዜ ጀምሮ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ...

Read More »

ቴዲ ማንጁስ ከቀድሞው የክልሉ ፕሬዝዳንት አብዲ ኢሌ ጋር ግንኙነት ነበረው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 26/2011)በሶማሌ በተፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶች የተጠረጠረው ቴዎድሮስ አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) ከቀድሞው የክልሉ ፕሬዝዳንት አብዲ ኢሌ ጋር ግንኙነት እንደነበረው ተገለጸ። በሶማሌ ክልል ከሐምሌ 26 እስከ 30/2010 ዓ.ም. ተፈጥሮ በነበረው  ግጭት ተጠርጥሮ የታሰረው አቶ ቴዎድሮስ አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) ከሌሎች ባለሥልጣናት ጋርም  ግንኙነት እንደነበረው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ለፍርድ ቤት ገልጿል፡፡ በሶማሌ ክልል ጅጅጋ ከተማ ግድያ፣ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት፣ ዘርን ...

Read More »