የአቶ መለስ ዜናዊን ከዚህ አለም በሞት መለየት ተከትሎ በገዢው ፓርቲ አባላት ና በሰራዊቱ ውስጥ በስፋት የቀጠለው ስብሰባ አሁንም ተጠናክሮል

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሳምንቱ መጀመሪያ ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው የመከላከያ ሰራዊት አባላትና የፌድራል ፖሊስ አባላት የጋራ ስብሰባ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በአፋር ክልል ተጀምሮዋል። በአፋር ክልል በሎጊያ ከተማ አባሐና በተባለው ሆቴል ባለፈው ቅዳሜ በተጀመረው ስብሰባ ከሻለቃ በላይ ማእረግ ያላቸው የመከላከያ ሰራዊት አዛዦችና የፌድራል ፖሊስ ሀላፊዎች መገኘታቸውን ከስፍራው የመጣው ዜና ያብራራል ። በአፋር ክልል ያለው አለመረጋጋትና የኢትዮጵያ ...

Read More »

እነ እስክንድር ነጋ በዛሬው ዕለት ፍ/ቤት ቀርበው ያለምንም ውጤት ተመለሱ

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበር ወጣቱ ፖለቲከኛ አቶ አንዱዓለም አራጌን ጨምሮ በአሸባሪነት የተከሰሱ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች በዛሬው ዕለት ፍ/ቤት ቀርበዋል፣ ያለምንም ውጤትም ወደ እስር ቤት ተመልሰዋል። ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ፣ አቶ አንዱዓለም አራጌ ፣ አቶ ናትናኤል መኮንን እንዲሁም አቶ ክንፈ ሚካኤል ደበበ እና ሌሎች በአሸባሪነት ተከሰው እስራት የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን በዛሬው ...

Read More »

በባድሜ ግንባር ኢሳትን ሲመለከቱ የተገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ታስረው ተፈቱ

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ አንድ ባለማእረግ መኮንን ከኢሳት ጋር ባደረገው ቃለምልልስ እንደገለጸው በክበባቸው ውስጥ በናይልሳት ቻናል የኢሳትን ዝግጅት ሲከታተሉ የተገኙ በርካታ ወታደሮች ከ14  ቀናት እስር በሁዋላ በከባድ ማስጠንቀቂያ ተለቀዋል። ወታደሮቹ የዲሻቸውን አቅጣጫ ወደ ናይል ሳይት ያዞሩት የውጭ ፊልሞችን ለመከታተል በማሰብ እንጅ ኢሳት የሚባል ጣቢያ መኖሩን በማወቃቸው አለመሆኑን ለአለቆቻቸው ተናግረው መፈታታቸውን መኮንኑ ተናግሯል። ...

Read More »

“ሆላንድ ካር” በኪሳራ ምክንያት ተዘጋ

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ከፍተኛ የመገናኛ ሽፋን አግኝቶ የነበረው በኢትዮጵያዊ እና በሆላንዳዊ በለሀብቶች የተቋቋመው የሆላንድ መኪና መገጣጠሚያ በኪሳራ ምክንያት መዘጋቱ ታውቋል። ኢትዮጵያዊው ኢንጂነር ታደሰ ተሰማ ከአንድ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የውጭ ምንዛሬ በተለይም የዶላር የምንዛሬ ዋጋ መዋዠቅ እና ታክስ ከፍተኛ ችግር ፈጥሮባቸው እንደነበር መግለጻቸው ይታወሳል። ጅጅጋ  ነው የተወለዱት።የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን እዚያው ካጠናቀቁ በሁዋላ  የሁለተኛ ...

Read More »

በህገ ወጥ መንገድ ተሰርተዋል የተባሉ ቤቶች አሁንም እየፈረሱ ነው።

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በዛሬው እለት በቦሌ ቡልቡላ ከ1ሺ በላይ በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን አካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። የፌደራል ፖሊስ አባላት የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲያንገላቱ መዋላቸውንም ነዋሪዎች ተናግረዋል። አንድ ቤታቸው የፈረሰባቸው ሰው ለኢሳት እንደተናገሩት በአሁኑ ጊዜ ህጻናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ቤት አልባ ሆነዋል። በእሳከሁኑ የመንግስት እርምጃ ከ30 ሺ በላይ ቤቶች እንደፈረሱ ይታመናል። በጉዳዩ ዙሪያ የመስተዳድሩን ባለስልጣናት ለማናገር ሙከራ ...

Read More »

ሰመጉ መንግስት የሚያደርሰውን ዜጎችን የማፈናቀል እርምጃ አወገዘ

ህዳር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ(ሰመጉ) ወይም በቀድሞው አጠራሩ ኢሰመጉ “ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የሚወሰድ ከመሬት የማፈናቀል እርምጃ የዜግነት መብቶችን ማሳጣት የለበትም” በሚል ርዕስ 122ኛውን ልዩ መግለጫ ዛሬ አወጣ፡፡ ሰመጉ በዚህ መግለጫው በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ ስላለው መልካም አስተዳደር ችግሮች፣የመብት ጥሰቶችና የሕዝብ ቅሬታ፣የታሰሩ ሰዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል፡፡ ከአዲስ አበባ ከተማ በሰሜን ምስራቅ በኩል 21 ኪሎሜትር ርቀት ...

Read More »

የመንግስት ጋዜጠኛው የሰራው የዜና ዘገባ ያለርሱ ፈቃድ ተቆራርጦ በቴሌቭዥን መቅረቡን አስታወቀ

ህዳር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ባልደረባ የሆነው ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ በጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2005 ዓ.ም የተካሄደውንና ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተሳተፉበት ውይይት አስመልክቶ በስፍራው በመገኘት ያጠናቀረው ፕሮግራም ያለአግባብ ተለውጦ እና ተቆራርጦ ለሕዝብ እንዲቀርብ መደረጉን አስታወቀ። ሰንደቅ ጋዜጣ ይህንኑ አስመልክቶ ዛሬ እንደዘገበው፣ ጋዜጠኛ አዲሱ መንገሻ በዋናነት በመልካም አስተዳደር፣ በተጠያቂነት እና በሙስና ችግሮች ላይ ...

Read More »

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለሁለተኛ ጊዜ ተዘረፈ

ህዳር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በአሁኑ ዝርፊያ ከ 50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት አጥቷል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የአይቲኤስሲ ላብራቶሪ ሰሞኑን ለሁለተኛ ጊዜ ተዘረፈ፡፡ ሪፖርተር ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ለሁለተኛ ጊዜ ሰሞኑን የተዘረፈው የ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢንስቲትዩቱ ላብራቶሪ እጅግ በጣም ውድ የሆኑ፣ የዘመኑን ቴክኖሎጂዎች ያካተቱና በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመቱ ንብረቶቹን አጥቷል። ዝርፊያው የተፈፀመው ...

Read More »

በዓለማችን የሠራተኞች መብት ከሚጣስባቸው ዋነኛ አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ ተገለፀ

ህዳር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ዓለም-አቀፉ የስራ ድርጅት ወይም ILO ኢትዮጵያ የሠራተኞች መብትና ጥቅም ባግባቡ ከማይከበርባቸው የዓለማችን አገሮች ከዋነኞቹ ረድፍ የምትመደብ መሆኗን አስታወቀ። ድርጅቱ ይህንኑ አስመልክቶ ሰሞኑን ያወጣው ሪፖርት እንደሚጠቁመው አርጀንቲና፣ ካምቦዲያ፣ ኢትዮጵያ፣ ፉጂ እና ፔሩ የሰራተኞችን መብት የሚጣስባቸው የዓለማችን አገሮች ናቸው በማለት ይኮንናቸዋል። ድርጅቱ ለዚህ እንደምሳሌ የጠቀሰው በገዥው ፓርቲ ጣልቃ ገብነት ዳግም የተቋቋመውን ተለጣፊውን የኢትዮጵያ ...

Read More »