በህገ ወጥ መንገድ ተሰርተዋል የተባሉ ቤቶች አሁንም እየፈረሱ ነው።

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:- በዛሬው እለት በቦሌ ቡልቡላ ከ1ሺ በላይ በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን አካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። የፌደራል ፖሊስ አባላት የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲያንገላቱ መዋላቸውንም ነዋሪዎች ተናግረዋል። አንድ ቤታቸው የፈረሰባቸው ሰው ለኢሳት እንደተናገሩት በአሁኑ ጊዜ ህጻናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ቤት አልባ ሆነዋል።

በእሳከሁኑ የመንግስት እርምጃ ከ30 ሺ በላይ ቤቶች እንደፈረሱ ይታመናል። በጉዳዩ ዙሪያ የመስተዳድሩን ባለስልጣናት ለማናገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide