የአንድነት ፓርቲ ልሳን “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ በአገሪቱ በየትኛውም ማተሚያ ቤት እንዳትታም ታገደች

ህዳር ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ  ጽህፈት ቤት የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው ህትመቷ ከታገደ በሁዋላ በቅርቡ ዳግም መታተም የጀመረችው ፍኖተ-ነፃነት  ከእንግዲህ በ አገሪቱ በሚገኝ በየትኛውም ማተሚያ ቤት እንዳትታተም  እገዳ ተጥሎባታል። ፓርቲው በወቅቱ አገራዊ ፖለቲካ ዙሪያ ነገ ህዝባዊ ስብሰባ የሚያካሂድ ሲሆን፤ በድርጅቲ ልሳን ላይ ስለተጣለው አዲስ እገዳ አስመልክቶ በስብሰባው ማብራሪያ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። በዋናነት የነገው ስብሰባ የተጠራው  በአገሪቱ ...

Read More »

አቶ በረከት ስምዖን በኢትዮጲያ ፖለቲካ ውስጥ ያላቸው ሚና እየጎላ መምጣቱ እየተነገረ ነው

ህዳር ፲፭ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ በረከት ስምዖን በኢትዮጲያ ፖለቲካ ውስጥ ያላቸው ሚና እየጎላ መምጣቱ በሕወሐት ሰዎች ዝንድ ቅሬታ መቀስቀሱና በአንዳንዶችም ዝንድ ቁጣ ማስከተሉ እየተሰማ ነው አቶ በረከትም ከጀርባ ሆነው ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ ወጥተው የፊት መስመር ላይ በግልፅ መታየት ጀምረዋል። በጠ/ሚ/ር ኋ/ማርያም ደሳለኝ የተመራ የልዑካ ቡድን ወደ ኬንያ ናይሮቢ በተጓዘበት ወቅት የልዑኩ 2ኛ ሰው ...

Read More »

አቶ በረሃነ ገ/ክርስቶስ የኢሕአዲግ አባላት ከሆኑት ዲፕሎማቶች ጋር ተወዛገቡ

ህዳር ፲፭ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተጠባባቂ ሚኒስትር አቶ በረሃነ ገ/ክርስቶስ የኢሕአዲግ አባላት ከሆኑት ዲፕሎማቶች ጋር መወዛገባቸውን የቅርብ ምንጮችን የጠቀሱ ዘገባዎች ይፋ አድርገዋል የውዝግቡ መነሻ የኢሕአዲግ አባላት ያልሆኑ ዲፕሎማቶች ለስራ በመታጨታቸው ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተጠባባቂ ሚንስትር  አቶ በረሃነ ገ/ክርስቶስ ከምክትላቸው ከአቶ ነጋ ፀጋዬ ጋር በመሩት ሥብሰባ ላይ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚቻል ደረጃ የኢሕአዲግ አባላት ...

Read More »

አልበሽር ላይ የታቀደው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መክሸፉን የሱዳን ባለሥልጣናት ይፋ አደረጉ

ህዳር ፲፭ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሱዳኑ ፕሬዝዳንት ጄነራል ኦማር ሐሰን አልበሽር ላይ የታቀደው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መክሸፉን የሱዳን ባለሥልጣናት ይፋ አደረጉ ። የሱዳኑ የቀድሞ የፀጥታ  ሃላፊ ሣላህ ጋሆሽን ጨምሮ 13 ሠዎች ከግልበጣው ሙከራ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውም ታውቋል። የሲዳን  የማስታውቂያ ሚኒስትር አሕመድ ቢላል ኦስማን ለዜና ሰዎች እንደተናገሩት ግልበጣው የታቀደው ላለፈው ሐሙስ እንደነበር አመልክተዋል ከሳምንት በኋላ ትናንት ...

Read More »

የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ታሪካዊ ሃውልት ተነስቶ ተመልሶ ይተካል የሚለውን ለመቀበል እንደሚቸገር ዲያቆን ዳንኤል ገለጸ

ህዳር ፲፭ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ከፒያሳ ተነስቶ፤ በመርካቶ በኩል አቋርጦ አብነት በታች የሚገኘው የኮካ ኮላ ፋብሪካ ጋር ይደርሳል ተብሎ የታሰበው የመጀመሪያው የባቡር ሃዲድ ዝርጋታ፣ በአጼ ኃይለ-ስላሴ ዘመነ መንግስት የተተከለውን የብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ለዘመናት ከነበረበት ስፍራ በቅርቡ እንደሚነሳ የአዲስ አበባ መስተዳድር አስታውቋል። ምንም እንኳን አሁን በይፋ ባይገለጽም የደብረ-ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት የሚገኘው የአጼ ምኒልክ ...

Read More »

በቤት ውዝግብ የተነሳ በሀረር አንድ አዛውንት ራሳቸውን ሰቅለው ገደሉ

ህዳር ፲፭ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ድርጊቱ የተፈጸመው ትናንት ህዳር 13 2012 ዓም ነው። በተለምዶ ጀጎል እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ለረጅም ጊዜ በቀበሌ ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩት የጥበቃ ሰራተኛው ባሻ ስዩም ተፈራ ባለፈው ዓመት ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ የቀበሌው ሹማምንት ይጠየቁዋቸዋል። ባሻ ስዩምም ዘመኔን በሙሉ የኖርኩበትን ቤት ትቼ መውደቂያ ሳይኖረኝ አልወጣም በማለት መልስ ሰጥተዋል። የክልሉ ባለስልጣናትም  በቅርቡ ቤታቸውን ብቻ ...

Read More »

በኦማር ሀሰን አልበሽር መንግስት ላይ የተደረገው የመፈንቅለ-መንግስት ሙከራ ከሸፈ።

ህዳር ፲፭ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በሱዳኑን የመፈንቅለ-መንግስት ሙከራ ሊያደርጉ የነበሩ የቀድሞው የ አገሪቱ የደህንነት ሀላፊ ሳላህ ጎሽ እና  ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ቢቢሲ ዘገበ። የ ዓይን ምስክሮች እንደተናገሩት ሀሙስ ማርፈጃውን    ታንኮችና ታጣቂዎችን የጫኑ የጦር ተሽከርካሪዎች የካርቱምን ጎዳና አጨናንቀዋት ውለዋል። ሱዳናውያን እያሻቀበ የመጣውን የኑሮ ውድነት በመቃወምና አስተዳደራዊ ለውጥ በመፈለግ በቅርቡ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን የዜና አውታሩ ...

Read More »

የግብጹ ፐሬዚዳንት ያወጡትን ህግ በመቃወም በካይሮ ሰልፍ ተደረገ

ህዳር ፲፭ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ፕሬዚዳንት ሙሀመድ ሙርሲ የቀድሞውን የግብጽ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ባለስልጣናትን ጉልበት ለመቀነስና አብዮቱን ለመጠበቅ በሚል ያወጡት አዲስ ህግ ከተቃዋሚዎች ሳይቀር ትችት እንዲሰነዘርባቸው አድርጓል። ፕሬዚዳንቱ ያወጡት መመሪያ በፍርድቤቶች ሳይቀር እንዳይቀለበስ ገድብ የሚጥል ነው። ታዋቂው ፖለቲከኛ ሙሀመድ ኤልባራዲ፣ ፕሬዚዳንት ሙርሲን ትንሹ ንጉስ ብለዋቸዋል። አዲሱን ህግ ተከትሎ በፕሬዚዳንቱ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች መካከል ግጭት መፈጠሩም ታውቋል። ___________________________________________________________________________________________________________________________________________________ ...

Read More »

የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አመራር አባላት የተመሰረተባቸው ክስ በአሸባሪነት የሚያስጠይቅ አይደለም ተባለ

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የልደታ ፍ/ቤትና አካባቢው በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ የሀወዝብ ብዛት ተጨናንቆ ማርፈዱም ተዘገበ። ዛሬ በልደታ ፍ/ቤት የቀረቡት የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ በአሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው 29 ሙስሊሞች ላይ አቃቢ ህግ የመሰረተው ክስ ተከሳሾቹን በአሸባሪነት አያስከስሳቸውም ሲሉ የተከሳሰሾቹ ጠበቆች አያስከስሳቸውም ያልዋቸውን ነጥቦች ለፍ/በቱ አቅርበዋል። በአሸባሪነት ህጉ አንቀፅ 3 እና 4 ተቀውሞአቸውን ያሰሙት የተከሳሾቹ ጠበቆች ...

Read More »

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልትሊፈርስ ነው

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በአዲስ አበባ የሚገኘው የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልትሊፈርስ ነው:፡ ዛሬ በሸገር ኤፍ ኤምላይ ቀርበው መግለጫ የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሀላፌ እንዳሉት ከባቡር ስራ ጋር በተያያዘ የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ይነሳል:: ሆኖም መነሳቱ በጊዜዊነት ነው ሀዲዱ ከተሰራ በሆላ ወደቦታው ይመለሳል ብለዋል:: የኢሳት ምንጮች ከፕሮጀክት መሀንዲሶች አካባቢ የተገኘን መረጃ ጠቅሰው እንደገለጡት የሀዲዱ ዲዛይን ላይ ለሚነሳው ...

Read More »