የወጪ ንግድ እያሽስቆለቆለ ነው ተባለ

ጥር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እጅግ በተለጠጠው የኢትዮጽያ መንግስት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሰረት በያዝነው 2006 በጀት ግማሽ ዓመት የወጪ ንግዱ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ማሽቆልቆል ማሳየቱን ያገኘናቸው መረጃዎች ጠቆሙ፡፡ በ2006 ግማሽ የበጀት ዓመት ከሆርቲካልቸር እና ከቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኤክስፖርት የተገኘው ገቢ ከዕቅዱ አንጻር እጅግ አነስተኛ መሆኑ አሳሳቢ ሆኗል፡፡ ከሆርቲካልቸር ዘርፍ ማለትም አበባ ፣አትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ለውጪ ገበያ ...

Read More »

መንግስት አንዳንድ ብቅ በማለት ላይ ያሉ ነጻ ጋዜጦችን ለመቅጨት እየሰራ ነው ተባለ

ጥር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የጋዜጦችና የመጽሔቶችን ስርጭት አስተካክላለሁ በሚል ያዘጋጀውን መጠይቅ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ለሚዲያዎችና ለአከፋፋዮች በማስሞላት ላይ ሲሆን ዋና አላማውም አንዳንድ ብቅ በማለት ላይ ያሉትን ነጻ ጋዜጦችን ለመቅጨት ያለመ ነው ተብሎአል፡፡ ከእንግሊዝ መንግስት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የሚካሄደው ጥናት መነሻ ” የጋዜጣና መጽሔት አከፋፋዮች ሕግና ስርዓትን ባልተከተለ መልክ ስርጭቱን በመያዝ መንግስት ...

Read More »

በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች የቤንዚን እጥረት ተከሰተ

ጥር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቤንዚንና የናፍጣ እጥረቱ በመላ አገሪቱ የተከሰተ ሲሆን በተለይም በአዲስ አበባ፣ በሶማሊ ክልል በጂጂጋ፣ ሀረርና ሌሎችም ከተሞች፣ በደቡብ ደግሞ በሃዋሳ ፣ ሆሳዕና ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሚዛን አማን መከሰቱን የደረሰን ዜና ያመለክታል። በጅጅጋ ከሁለት ቀናት በሁዋላ  ነዋሪዎች ነዳጅ ለመቅዳት ሲጋፉ ታይቷል። ችግሩ የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣታቸውና ነዳጁን ማከፋፈል በማቆማቸው የተፈጠረ ...

Read More »

ሱዳንና ግብጽ ወታደራዊ ግንኙነታቸውን ለማጠንከር ተስማሙ

ጥር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግብጹ ወታደራዊ አዛዥ እና የአገሪቱ መሪ ማርሻል አብደል ፋታህ አል ሲሲ ከሱዳን የመከላከያ ሚኒስትር አብደል ራሂም ሙሃመድ ሁሴን ጋር ወታደራዊ ግንኙነቱን ለማጠንከርና የጋራ ድንበሮቻቸውን ለመጠበቅ መስማማታቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል። ሚኒስትር ሁሴን ካይሮ በመሄድ የግብጹን ወታደራዊ መሪ ያገኙ ሲሆን፣ ሁለቱ አገራት የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ለማድረግ ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ የሱዳኑ ወታደራዊ አዛዥ እንደገለጹት ...

Read More »

የቡራዩ ነዋሪዎች ፌደራል ፖሊስ ከአካባቢው እንዲወጣ እየጠየቁ ነው

ጥር ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ልዩ ዞን በቡራዩ ከተማ ትናንት የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የአካባቢው ህዝብ የፌደራል ፖሊሶች በከተማዋ ወጣቶች ላይ የሚፈጽሙት ተደጋጋሚ ግድያ፣ የጸጥታ ስጋት ስለፈጠረብን አካባቢውን ለቆ ይውጣ በማለት መጠየቃቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመልክቷል። የመንግስት ባለስልጣናት በበኩላቸው ገዳይ የፌደራል ፖሊሶችን ለፍርድ እናቀርባለን በማለት ህዝቡን ለማረጋጋት እየሞከሩ ነው። በህዝቡና በፌደራል ፖሊስ መካከል ግጭቱ የተነሳው ከትናንት ...

Read More »

በደቡብ እና ምስራቅ ኢትዮጵያ አሰቃቂ ረሀብ መከሰቱ ተዘገበ

ጥር ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን በመጥቀስ እንደዘገቡት በደቡብ እና ምስራቅ ኢትዮጵያ አስከፊ ረሀብ መከሰቱን ተከትሎ የህዝቡ ህልውና አደጋ ውስጥ ወድቋል። የሲኤን ቢሲ ዘጋቢ እንደገለጸው ችግሩን ለመቅረፍ እስከ 100 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ ያስፈልጋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የያዘው የምግብ ክምችት ማለቁንም በዘገባው ተገልጿል። እንደ ሲኤን ቢሲ ዘገባ በአፍሪካ ወደ 14 ሚሊዮን የሚጠጋ ...

Read More »

የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ

ጥር ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የታሳሪ ቤተሰቦች፣ የሚዲያ ባለሞያዎችና የውጭ አገራት ዲፕሎማቶች  በተገኙበት በተካሄደው ችሎት  የታሳሪ ጠበቆች የምስክሮቻቸውን አድራሻ አሟልተው አለማቅረባቸው በፍርድ ቤቱ ተገልጿል። ጠበቆቹ የምስክሮችን ስም በፍጥነት ለማስታወቅ ያልቻሉት ጂሃዳዊ ሐረካት ፊልም ለህዝብ መለቀቁን ተከትሎ በምስክሮች ላይ ፍርሀት በማደሩና የተለያዩ አካላት ስለሚያስፈራሯቸው ለደህንነታቸው በመስጋታቸው መሆኑን እንዲሁም የሰነድና የቪዲዮ ማስረጃዎች ለማቅረብ ደግሞ ተጨማሪ ጊዜ የሚያስፈልግ መሆኑን ...

Read More »

አቶ በረከት ስምኦን ኢህአዴግን በመድብለ ፓርቲ ስም ለርጅም ጊዜ እንዲሄድ ማድረግ እንደሚገባ ገለጹ

ጥር ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሚዲያ ዝግ በመሆን ለኢህአዴግ ካድሬዎችና ሹሞች በተዘጋጀው ውይይት ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የሆኑት አቶ በረከት ስምኦን  በኢትዮጵያ በልማታዊ አጀንዳ የሚወከለው ኢህአዴግ ብቻ ነው ያሉ ሲሆን፣ ሌሎች ፓርቲዎች ወይ ይህንን የሚጻረሩ ናቸው፣ ወይም ትርጉም የሌላቸው ናቸው ብለዋል።  ኢህአዴግ ለረጅም ጊዜ  በስልጣን ላይ ለማስቀጠል በመድብለ ፓርቲ ስም ይዞ መጓዝ እንደሚጠቅም አቶ በረከት ተናግረዋል። ...

Read More »

ሁለት የኬንያ ፖሊሶች ከኦጋዴን ነጻ አውጭ ባለስልጣናት ጠለፋ ጋር በተያያዘ ታሰሩ

ጥር ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኬንያ መንግስት ጋባዥነት ከኢህአዴግ መንግስት ጋር ድርድር ለማድረግ በናይሮቢ የተገኙት ሁለቱ የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት አመራሮች አቶ ሱሉብ አህመድና አቶ አሊ ሁሴን ተጠልፈው ወደ ኢትዮጵያ መወሰዳቸውን የኬንያ መንግስት ባስታወቀ ማግስት፣ ሁለት ለኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች ተቀጥረው ይሰሩ ነበር የተባሉ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር ውለዋል። ባለሰልጣኖቹ ለምሳ ተጋብዘው በመጓዝ ላይ እንዳሉ ቆመው ይጠብቋቸው በነበሩ ...

Read More »

በቦዲና በኮንሶ ብሄረሰቦች መካከል በተነሳው ግጭት የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ

ጥር ፳፮ (ሃያ ስድት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግጭቱ የተከሰተው ባለፈው ሳምንት ሲሆን፣ ለግጭቱ መነሻ የሆነውም ኮንሶዎች ባጋጠማቸው የመሬት እጥረት ሳቢያ ወደ ቦዲዮች አካባቢ ሄደው በመስፈራቸው መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ይገልጻሉ። በግጭቱ ከሁለቱም ወገኖች 4 ሰዎች ሲሞቱ፣ 3 ኮንሶዎች እና አንድ ፖሊስ ቆስለዋል። 72 ቤቶችም እንዲሁ ተቃጥለዋል። ከዚህ በፊት ሁለቱ ብሄረሰቦች በተደጋጋሚ ሲጋጩ ቆይተዋል። ቀደም ሲል መንግስት የኮንሶ ሰፋሪዎችን ወደ ...

Read More »