ኦነግ በሰኔ 16ቱ የቦምብ ጥቃት እጄ የለበትም አለ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 8/2011)በአዲስ አበባ ከተማ ሰኔ 16/2010 በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ላይ በተቃጣው የግድያ ሙከራ እጁ እንደሌለበት ኦነግ ገለጸ። ኬንያ ሆና ድርጊቱን በማቀነባበር የተጠረጠረችው ግለሰብ አባላችንም ሆነ ደጋፊያችን አይደለችም ሲሉ የግንባሩ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ተናግረዋል። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር/ኦነግ/ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ከ25 አመታት በፊት በበደኖ ከተማ በኦነግ ተፈጸመ የተባለውን አሰቃቂ ግድያ አስተባብለዋል። ገለልተኛ መርማሪ አካል እንዲቋቋም ያኔም ጥያቄ ...

Read More »

በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት አደጋ ላይ ወድቋል ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 28/2011)በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት አደጋ ላይ በመውደቁ ሕግ የማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ እንደሚፈጸም ተገለጸ። አወዛጋቢ የሆኑትና በአፋኝነታቸው የሚጠቀሱ አዋጆች በዚህ አመት እንዲሻሻሉ ዝግጅት መጠናቀቁም ተመልክቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2011 አዲስ አመት የመጀመሪያ ስብሰባውን ሲያደርግ የተገኙት ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ ባደረጉት ንግግር እንዳመለከቱት የፖለቲካ ምህዳሩን የማስፋቱ ስራም ተጠናክሮ ይቀጥላል። በየአካባቢው ያለውን ግጭትና የተከተለውን የሰዎች ሞት የዘረዘሩት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ የሕግ የበላይነት ...

Read More »

ከ900 ዓመታት በላይ ያስቆጠሩት የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመታደግ ከ 10 ዓመት በፊት የተሰራው የጸሀይ እና የንፋስ መከላከያ ጣሪያ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እያመዘነ መምጣቱን የደብሩ መነኮሳት እና የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ

ከ900 ዓመታት በላይ ያስቆጠሩት የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመታደግ ከ 10 ዓመት በፊት የተሰራው የጸሀይ እና የንፋስ መከላከያ ጣሪያ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እያመዘነ መምጣቱን የደብሩ መነኮሳት እና የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ ( ኢሳት ዜና መስከረም 28 ቀን 2011 ዓ/ም ) ነዋሪዎቹ ባካሄዱት ትዕይንተ ህዝብ ላይ የደብሩ አስተዳዳሪዎች እንዳሉት ለ 5 ዓመት ተብሎ የተሰራው ከፍተኛ ክብደት ያለው ጊዚያዊ ጣሪያ ከጥቅሙ ይልቅ ...

Read More »

የጣቁሳ ወረዳ መምህራን የስራ ማቆም አድማ አደረጉ

የጣቁሳ ወረዳ መምህራን የስራ ማቆም አድማ አደረጉ ( ኢሳት ዜና መስከረም 28 ቀን 2011 ዓ/ም ) በማእከላዊ ጎንደር ዞን በጣቁሳ ቀረዳ የሚገኙ ከ70 በላይ በሚሆኑ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ የወረዳው መምህራን የስራ ማቆም አድማ ያደረጉት ከቤት መስሪያ ቦታ ጋር በተያያዘ ከማዘጋጃ ቤቱ ጋር በተፈጠረ ችግር ነው። መንግስት ባወረደው መመሪያ መሰረት በ24 ማህበራት የተደራጁ መምህራን ቦታ ይሰጠናል ብለው ሲጠባበቁ ምንም መልስ ባለማግኘታቸው ...

Read More »

ዶ/ር አብይ አህመድና አቶ ደመቀ መኮንን ኢህአዴግን እንዲመሩ በድጋሜ ተመረጡ

ዶ/ር አብይ አህመድና አቶ ደመቀ መኮንን ኢህአዴግን እንዲመሩ በድጋሜ ተመረጡ ( ኢሳት ዜና መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ/ም ) በሃዋሳ በመካሄድ ላይ ባለው የኢህአዴግ ጉባኤ ዶ/ር አብይ አህመድ ድምጽ ከሰጡ 177 ሰዎች ውስጥ የ176 ሰዎችን ድምጽ በማግኘት ሊቀመንበር ሆነው ሲመረጡ፣ አቶ ደመቀ መኮንን ደግሞ 149 ድምጽ በማግኘት ምክትል ጠ/ሚኒስትር ሆነው ተመርጠዋል። የህወሃት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል 15 ድምጽ በማግኘት የምክትል ...

Read More »

በአፍ መፍቻ ቋንቋችን እንድንማር ይፈቀድልን ያሉ የራያ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቆሙ። በአድማው 23 ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል።

በአፍ መፍቻ ቋንቋችን እንድንማር ይፈቀድልን ያሉ የራያ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቆሙ። በአድማው 23 ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። ( ኢሳት ዜና መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ/ም ) በዘንድሮ የ2011 ዓ.ም አዲሱ የትምህርት ዘመን ወደ ትምህርት ገበታቸው መግባት የነበረባቸው የራያ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋችን ካልሆነ አንማርም ማለታቸውን ተከትሎ ከ1ኛ እስከ 2ኛ ደረጃ ያሉ ትምህት ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ዝግ ሆነዋል። ሕዝቡ በህገመንግስቱ የተሰጠን መብት የትግራይ ...

Read More »

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በድህረ ምርቃ ተማሪዎች ከፍያ ላይ 125 በመቶ የክፍያ ጭማሪ አደረገ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በድህረ ምርቃ ተማሪዎች ከፍያ ላይ 125 በመቶ የክፍያ ጭማሪ አደረገ ( ኢሳት ዜና መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ/ም ) ተማሪዎቹ ለኢሳት በላኩት መረጃ እንዳመለከቱት ዩኒቨርስቲው በድህረ ምረቃ ተማሪዎች ክፍያ ላይ 125 በመቶ ጭማሪ በማድረጉ በኑሮአቸው ላይ ጫና ፈጥሯል። ለጥናት ወረቀት ወይም ፕሮጀክት በክሬዲት 600 የሚክፍሉ ሲሆን ለ30 ክሬዲት እስከ 18 ሺ ብር ይከፍላሉ። ተማሪዎቹ የክፍያ መጠናቸው አቅምን ...

Read More »

የኖቤል ሽልማት ተሸላሚዎች ታወቁ

የኖቤል ሽልማት ተሸላሚዎች ታወቁ ( ኢሳት ዜና መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ/ም ) ይህ ሽልማት የ25 ዓመቷን ወጣት ወ/ሮ ናዲያ ሙራድን የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማትን በወጣትነቷ ያገኘኝ ሁለተኛዋ እንስት መሆን አስችሏታል። ባለፈው ተመሳሳይ ዓመት የ17 ዓመቷ ፓኪስታኒያዊቷ ወጣት ማላላ ዩሳፊዛይ የ2017 እ.ኤ.አ. ሽልማትን ማግኘቷ ይታወሳል። የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ ተወላጅ የሆኑት የ63 ዓመቱ ዶ/ር ዴኒስ ሙክዌጌ በበኩላቸው ለበርካታ ዓመታት በእርስበእርስ ...

Read More »

የኖቤል አሸናፊዎች ታወቁ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 25/2011) የ2018 የሰላም ኖቤል አሸናፊዎች ታወቁ። የዘንድሮው የሰላም ኖቤል አሸናፊወቹ  ዶክተር ዴኒስ ሙክዌጄ የተባሉ ኮንጎአዊ እና ናዲያ ሙራድ የተባለች ኢራቃዊ መሆናቸው ይፋ ተደርጓል። ሁለቱም የሰላም ኖቤል አሸናፊዎች በግጭትና ጦርነት አካባቢዎች ወሲባዊ ጥቃት እንዲቆም በሰሯቸው ተግባራት መመረጣቸው ታውቋል። የሰላም ኖቢል ሽልማቱን በጋራ ካሸነፉት መካከል የኮንጎ ዜግነት ያላቸው ዶክተር ዴኒስ ሙክዌጄ የማህፀን ሀኪም ናቸው። ዶክተር ዴኒስ ህክምና በመስጠትም ይታወቃሉ። በዲሞክራቲክ ...

Read More »

የፊልምና ቴአትር ቅድመ ገምገማ ተነሳ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 25/2011) በፊልምና ቴአትር ላይ ይደረግ የነበረው ቅድመ ገምገማ ተነሳ ። የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዛሬ በደብዳቤ እንዳሳወቀው ቅድመ ግምገማውን ይደግፉ የነበሩ አሰራሮችና መመሪያዎች ከህገመንግስቱ በታች ስለሆኑ ከመከረም 26 ጀምሮ አሰራሩ መነሳቱን አሳውቋል። በአዲስ አባባ በህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ በረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዮ ፊርማ የወጣው ደበዳቤ እንደሚናገረው የፊርማና የግል የቴአትር ስራዎች ከመታየታቸው በፊት ተገምግመው ማሳያና ማሰራጫ ፈቃድ ያላገኙ ...

Read More »