በቴፒ አቅራቢያ ከፍተኛ ውጊያ ተካሄደ- ታጣቂዎች ፖሊስ ጣቢያ ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል

ግንቦት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጋምቤላና ደቡብ ክልል አዋሳኝ ከተማ በሆነቸው ቴፔ ትናንት ሌሊት 11 ሰአት ላይ ለተሻለ ፍትህና ነጻናት እንታገላለን የሚሉ ታጣቂዎች በአንድ የፖሊስ ጣቢያ ላይ በወሰዱት እርምጃ 3 የሌሊት ተረኛ ፖሊሶች ሲገደሉ በርካታ እስረኞችንም አስፈትተዋል። ቁጥራቸው ከ100 እስከ 150 የሚሆኑ በቴፒና አካባቢው የሚታየውን ዘረኝነትና የአስተዳደር በደል እንዋጋለን በማለት ራሳቸውን አደራጅተው ጫካ የገቡ ወጣቶች ባለፉት ...

Read More »

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ክስ ተመሰረተባቸው

ግንቦት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ያለፉትን 9 ወራት በእስር ሲማቅቁ የቆዩት የሰማያዊ፣ የቀድሞው አንድነትና የመኢኢድ ፓርቲዎች የአመራር አባላት ላይ ክስ መመስረቱን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። በአንደኛ ተከሳሽ ጌታቸው መኮንን መዝገብ 16 ሰዎች በሽብር ወንጀል መከሰሳቸውን ጋዜጣው ዘግቧል። ተከሳሾቹ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን ፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ፣ አወቀ ሞኝሆዴ፣ ዘሪሁን በሬ፣ ወርቅየ ምስጋና፣ አማረ መስፍን፣ › ተስፋዬ ...

Read More »

በመርካቶ የደረሰው ቃጠሎ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ

ግንቦት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እኩለቀን ላይ ሸራ ተራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የተነሳው ቃጠሎ በርካታ የንግድ ቤቶችን አውድሟል። የእሳት ማጥፋያ መኪኖች እሳቱን ለመቆጣጠር ጥረት ቢያደርጉም፣ ይህን ዘገባ እስካጠናከርንበት በኢትዮጵያ ከቀኑ 11 ሰአት ድረስ እሳቱ በቁጥጥር ስር አልዋለም። ዘጋቢያችን እንደገለጸው በቃጠሎው ከፍተኛ ንበረት ሳይወድም አልቀረም። የእሳቱ መንስኤ በውል አለመታወቁንም ገልጿል።

Read More »

በኢትዮጵያ ሶማሊያ ድንበር በተነሳው ግጭት የመከላከያ ሰራዊት አባላት የገደሉዋቸው ሰዎች ቁጥር ጨምሯል

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምንጮች እንደገለጹት የሶማሊ ክልል ልዩ ሚሊሺያ አባላትና የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በወሰዱት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አልቀዋል። ሂራን በተባለው አካባቢ ለቀናት በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት መንስኤ በውል አልታወቀም። ዛሬ በማህበራዊ ድረገጾች የተላለፈው አስደንጋጭ ቪዲዮ በርካታ የሞቱ ሲቪሎችንና የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ያሳያል። ቪዲዮውን የለቀቀው የአልጃሲራ ኒውስ ሶማሊያ ወኪል ለኢሳት እንደገለጸው ...

Read More »

በኢትዮጵያ ባለፉት 5 ዓመታት ብቻ ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ወደ ውጭ ተሻግሯል

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግሎባል ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ ባወጣው ልዩ ዘገባ በፈረንጆች አቆጣጠር ከ2008 እስከ 2012 ባለው ጊዜ ውስጥ ከኢትዮጵያ በተለያዩ ህገወጥ መንገዶች ከ70 በሊዮን ብር ወይም ከ3 ቢሊዮን 550 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ወደ ውጭ ወጥቷል። በ5 ዓመታት ውስጥ ተሰርቆ የወጣው ገንዘብ ወደ አገሪቱ ከገባው የውጭ የቀጥታ ኢንቨስትመንት መጠን ጋር ሲተያይ በ1 ሺ 355 በመቶ ...

Read More »

የዶላር እጥረቱ ተባብሶ ቀጥሎአል

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የሚታየው ከፍተኛ የዶላር እጥረት መባባሱን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።በአስመጭና ላኪነት ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ስራቸውን መስራት እንዳልቻሉ አቤቱታ በማቅርብ ላይ ናቸው። በርካታ ፋብሪካዎችም በዶላር እጥረት የተነሳ የመለዋወጫ እቃዎችን ማስገባት አለመቻላቸውን እየገለጹ ነው። መንግስት የዶላር ችግር እንደሌለ በተደጋጋሚ ቢናገርም፣ በመሬት ላይ ያለው እውነታ ከዚህ እንደሚለይ ነጋዴዎች ይገልጻሉ። ለኢሳት የሚደርሱት መረጃዎች እንደሚያሳዩት በአንዳንድ ...

Read More »

በጀርመን የኢትዮጵያ ኢምባሲ የተዘመረው መዝሙር ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጠረ

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው የግንቦት20 በአልን ለማክበር ጀርመን በርሊን ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ ያልተጠበቀ ክስተት መታየቱን ምንጮች ገልጸዋል። በዝግጀቱ ላይ የኢትዮጵያና የጀርመን ከፍተኛ ባለስልጣናት በእንግድነት ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ መዝሙር ያለምንም ችግር የተፈጸመ ቢሆንም፣ የጀርመን ብሄራዊ መዝሙር በሚዘመርበት ጊዜ ግን የጀርመንን ባለስልጣናት ያስደነገጠ መዝሙር ቀርቧል። የኢትዮጵያ ኢምባሲ የጀርመን ብራሄራዊ መዝሙር ብሎ ያቀረበው ...

Read More »

በአቶ አሊ መኪ ላይ የ 15 አመት ፅኑ እስራት ተፈረደበት

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ አሊ በኡስታዝ አቡበክር አህመድ መዝገብ ተከሶ የሚገኝ ሲሆን፣ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ፣ በሌሉበት የ15 አመት ጽኑ እስራት ፈርዶባቸዋል። ታህሳስ 23/2005 የዋለው ችሎት አቶ አሊን በነጻ ቢያሰናብታቸውም፣ አቃቢ ህግ ይግባኝ ብሎባቸው ክሱ እንደገና እንዲታይ ተደርጓል። በአቶ አሊ ላይ የተሰጠው ውሳኔ በሌሎች የድምጻችን ይሰማ የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላት ላይ ሊሰጥ የታሰበውን ...

Read More »

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በ2006 በጀት ዓመት ያለምንም ማስረጃ ገንዘብ ከሚያወጡ መንግስታዊ ተቋማት መካከል የደህንነት ተቋም ዋንኛው መሆኑን አጋለጠ፡፡

ግንቦት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዋና ኦዲተር የ2006 ዓ.ም የመንግስት መ/ቤቶች የሂሳብ ሪፖርት ትላንት ለፓርላማው ያቀረበ ሲሆን በዚህ ሪፖርቱ ያለምንም ማስረጃ ገንዘብ ያወጡ 19 መንግስታዊ ተቋማት የተገኙ ሲሆን እነዚህ ተቋማት በድምሩ ከ473 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አውጥተው ተገኝተዋል፡፡ ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ላቅ ያለውን ድርሻ ማለትም 274 ሚሊየን ብር ያወጣው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መሆኑን ሪፖርቱ ያሳያል፡፡ ...

Read More »

በኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች ተጠልፈው የነበሩት የኦብነግ ባለስልጣናት በኬንያ መንግስት እና በአለማቀፍ ማህበረሰብ ጥረት መፈታታቸውን ግንባሩ አስታወቀ

ግንቦት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦጋዴን ነጻ አውጭ ግንባር ለኢሳት በላከው መግለጫ ፣የኦብነግ ሁለቱ ተደራዳሪዎች አቶ ሱሉብ አህመድና አቶ አሊ ሁሴን ፣ እኤአ ሰኔ 1 ቀን 2015 በኢትዮጵያ የደህንነት ባለስልጣን አጃቢነት የኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር ከተማ የሆነችው ሞያሌ ደርሰዋል። ሁለቱ ልኡካኖች ናይሮቢ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተገናኝተዋል። ኦብነግ ተወካዮቹ በኬንያ መንግስት እና በአለማቀፍ ማህበረሰብ ጥረት መለቀቃቸውን ገልጾ ፣ ...

Read More »