በመርካቶ የደረሰው ቃጠሎ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ

ግንቦት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እኩለቀን ላይ ሸራ ተራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የተነሳው ቃጠሎ በርካታ የንግድ ቤቶችን አውድሟል። የእሳት ማጥፋያ መኪኖች እሳቱን ለመቆጣጠር ጥረት ቢያደርጉም፣ ይህን ዘገባ እስካጠናከርንበት በኢትዮጵያ ከቀኑ 11 ሰአት ድረስ እሳቱ በቁጥጥር ስር አልዋለም።
ዘጋቢያችን እንደገለጸው በቃጠሎው ከፍተኛ ንበረት ሳይወድም አልቀረም። የእሳቱ መንስኤ በውል አለመታወቁንም ገልጿል።