በደቡብ ክልል በርካታ ከተሞች አርበኞች ግንቦት7 የድጋፍ ወረቀቶች ተበተኑ

ኀዳር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ያነጋገራቸው ወጣቶች እንደገለጹት፣ በወላይታ ሶዶ ከ1 ሺ የማያንሱ በራሪ ወረቀቶች ተበትነዋል። ራሳቸውን ያደራጁት ወጣቶች በፖሊስ፣ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶችና የገበያ ማእከላት የአርበኞች ግንቦት7 ሊ/መንበር የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ን ፎቶ እንዲሁም የቅስቀሳ መልእክቶችን የያዙ ወረቀቶችን በግድግዳዎች ላይ ለጥፈዋል። ፖሊሶች ወረቀቶችን በመቅደድ ተጠምደው ማርፈዳቸውን፣ በከተማው ውስጥ ትልቅ የመነጋገሪያ ርእስ መፍጠሩንም ወጣቶች ለኢሳት ...

Read More »

የመንግስት ደህንነቶች የኢሳትን ዌብሳይት ሰብረው ለመግባት ያደረጉት ሙከራ ከሸፈ

ኀዳር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የመረጃ ደህንነት ባለሙያዎች በማስረጃ አስደግፈው እንደገለጹት የኢህአዴግ የመረጃ ደህንነት ሰራተኞች መብራቱ በሚል ስም ኢሳት በኢንተርኔት የሚያሰራጨውን ዌብሳይት ሰብረው በመግባት፣ ጉዳት ለማድረስ በተደጋጋሚ ቢሞክሩም ሳይሳካላቸው ቀርቷል። የኮምፒዩት መለያ ቁጥሩ 197. 156. 86. 162 የሆነ አዲስ አበባ የሚገኝ ኮምፒዩተር መብራቱ በሚል የመግቢያ ስም ወደ ወደ ኢሳት ዌብሳይት ለመግባት ቢሞክርም አልተሳካለትም። መንግስት በሚሊዮን ...

Read More »

በቴፒ ከተማ ውጥረት ነግሷል

ኢሳት (ህዳር 14 ፣ 2008) በደቡብ ምዕራብ ቴፒ ከተማ የተቀሰቀሰውን አስተዳደራዊ አለመግባባት ተከትሎ ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ የፌዴራል ፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት አባላት በአካባቢው መስፈሩ ተገለጠ። በከተማዋ ላይ የተነሳው የይገባኛል አስተዳደራዊ ጥያቄ ስምምነት ባለማግኘቱ በርካታ ሰዎች በተቃውሞ ጫካ መግባታቸውንና ድርጊቱ በከተማዋ ውጥረት ማንገሱን በሃገር ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ከሚዛን ተፈሪ ወደ ቴፒ፣ ከሸሸንዳ ከተማ ወደ ቴፒ፣ ከሚሻ ከተማ ...

Read More »

ድርቁ ከ1977ቱ ያልተናነሰ ነው ሲሉ አርሶአደሮች ተናገሩ

ኀዳር ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በወሎ፣ቆቦና ዋግ ህምራ አካባቢ የሚኖሩ አርሶ አደሮች የዘንድሮው ድርቅ ከ1977ቱ ያልተለየ ነው በማለት ለኢሳት ተናገሩ፡፡ ተጎጂዎች በድርቁ በርካታ ሃብት ንብረታቸውን በመጨረሳቸው ባዶ እጃቸውን እንደቀሩ ይናገራሉ፡፡የገዢው መንግስት ሚዲያዎች በድርቁ የሞተ ሰው የለም በማለት ለማስተባበል ቢሞክሩም ተጎጅዎቹ ‹‹ ከሃብታችን ባሻገር ልጆቻችን እየተነጠቅን ነው፡፡ ›› በማለት በተጨባጭ ያለውን የወቅቱን ችግር ይገልጻሉ፡፡ ድርቁ ዘንድሮ በይፋ ...

Read More »

ኢትዮጵያ ወደ ኬንያ የሚወስዱ መንገዶችን ዘጋች

ኀዳር ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው አርብ በኬንያ ፖሊስና እና በኢትዮጵያ ወታደሮች መካካል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ 3 የኬንያ ፖሊሶች እና 4 የኢትዮጵያ ወታደሮች መገደላቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያ ወደ ኬንያ የሚወስዱ መተላለፊያ መንገዶችን ዘግታለች። ሞያሌ፣ ሶሎሎ፣ ፎሮሌ፣ ዱካና እና ኢሌሪቲ የተባሉት የድንበር መተላለፊያዎች ተዘግተዋል። የኢትዮጵያ ወታደሮች የኦነግ ታጣቂዎችን ለመዋጋት በሚል ወደ ኬንያ በመግባታቸው የተኩስ ልውውጡ ተደርጓል። በድንበር አካባቢ ...

Read More »

የእስራኤል መንግስት የመጨረሻ ዙር ቤተ እስራኤላዊያን ወደ አገሩ እንዲገቡ ፈቀደ

ኀዳር ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለብዙ ዓመታት ከቤተሰቦቻቸው ተነጥለው ሲጉላሉ የነበሩት 9 ሽህ ቤተ-እስራኤላዊያን ወደ እስራኤል እንዲገቡ በእስራኤል መንግስት ፍቃድ ማግኘታቸው እንዳስደሰታቸው በተስራኤላዊያኑ ተናግረዋል።እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ከ1970 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ እስራኤል እንዲገቡ የተፈቀደላቸው ቤተ እስራኤላዊያን ከሰላሳ ዓመታት በላይ በተለያዩ ሁኔታዎች ጉዟቸው መደናቀፉ ያሳዘናቸው ሲሆን ዘግይቶም ቢሆን ውሳኔ መሰጠቱን በጸጋ ተቀብለውታል። ትውልደ ኢትዮጵያዊያኑ ኢትዮ-እስራኤላዊያን በእስራኤል ማኅበረሰብ መድሎና ...

Read More »

የጉጂ ማህበረሰብ አባላት ህዝባዊ እምቢተኝነት ለመጀመር እየተዘጋጀን ነው አሉ

ኀዳር ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በጉጂ ዞን የሚኖሩ የተለያዩ ብሄረሰቦች በአንድ ላይ በመሆን ያቀረብነው የመልካም አስተዳደር እና የፍትህ ጥያቄ ካልተመለሰ የህዝባዊ እምቢተኝነት ተቃውሞአቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። የዞኑ የአገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎችና የአካባቢው ባለስልጣናት በአንድነት ሆነው ኦሮምያ ክልል በመሄድ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ መልስ ሊያገኙ አልቻሉም። ጥያቄያቸውን ይዘው ወደ ጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ማምራታቸውንም ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ለኢሳት ገልጸዋል። አስተባባሪዎች ...

Read More »

በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች ዜጎች በምግብ እጥረት እየተሰቃዩ ነው

ኀዳር ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአለማቀፍ ድርጅቶች ችግሩ አሳሳቢ መሆኑን እየገለጹ ሲሆን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ችግሩ አስከፊ ሆኖ ቀጥሎአል። በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ አርብቶአደሮች በድርቅ፣ ከግልገል ጊቤ ግድብ ግንባታና በአካባቢው የተነሳውን ግጭት ተከትሎ ከመከላከያ ሰራዊት በሚደርሰው ጥቃት፣ ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውን የደቡብ ኦሞ ህዝብ ድርጅት ምክትል ሰብሳቢ አቶ አለማየሁ መኮንን ተናግረዋል።በአማራ ክልል በተለይ በሰሜን ወሎ አካባቢ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ...

Read More »

ብአዴን የባጃጅ አሽከርካሪዎች ሰልፍ እንዲወጡ ሲያሳድድ እንደነበር ተገለጸ

ኀዳር ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህዳር 9፣ 2008 ዓም ብአዴን በሰልፉ ለመሳተፍ የሚፈልገውን አሽከርካሪ ማግኘት ባለመቻሉ የባጃጅ ማህበር አመራሮችን በመንገድ ትራንስፖርት አማካኝነት በመጥራት በሰልፉ ባይሳተፉ የአምስት መቶ ብር ቅጣት እንደሚፈጽም በማስፈራራት ከቀኑ 10፡30 እስከ 11፡30 መንገዶችን በመዘጋጋት ህብረተሰቡን ሲያስጨንቅና ባጃጆችን ተሰለፉ በማለት ሲያሳድድ እንደነበር ዘጋቢያችን ገልጻለች። የባህርዳር ነዋሪዎች ብአዴን በዓሉን ብቻውን እያከበረ መሆኑን ያየንበት ክስተት ነው ብለዋል። ...

Read More »

የብአዴን ታጋዮች የሞትንለት እና የደማንለት ድርጅት አክስሮናል አሉ፡፡

ኀዳር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ብአዴን ህዳር 11 በባህርዳር በሚያከብረው በአል ላይ ለነባር ታጋዮች ልዩ የሽልማት ስነስርዓት ያዘጋጀ ሲሆን፣ ለሽልማቱ የታጩት አመራሮች በድርጅት ነባር አባላት አስተያየት እንዲሰጥባቸው ማድረጉን ተከትሎ፣ ነባር ታጋዮቹ በብአዴን አመራሮች ላይ የሰላ ትችት አቅርበዋል፡፡ ታጋዩች ከድል በሁዋላ እስከ ሜጀር ጀኔራልነት የሚደርስ ማዕረግ ቢሰጠንም ከመዝገብ ቤት ያለፈ የውሳኔ ሰጭነት ስልጣን የለንም ብለዋል፡፡ ነባር አባሎቹ “ብአዴን ...

Read More »