አምነስቲ ኢንተርናሽናል መላው ዓለም በእስር ቤት ያሉትን ኢትዮጵያዊያን ጋዜጠኞችን እንዳይዘነጋ ጥሪውን አቀረበ

ኀዳር ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ቀንን ምክንያት በማድረግ ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል በሽብር ሕግ ተከሶ ከአራት ዓመታት በላይ በእስር የሚማቅቀውን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ ካለ ወንጀላቸው ከስራ ገበታቸው ታፍነው በወሕኒ የሚማቅቁትን ኢትዮጵያዊና ጋዜጠኞችንና የሰብዓዊ መብት ተሟጓቾችን መላው ዓለም ለአፍታም ሊዘነጋቸው እንደማይገባ መግለጫ አውጥቷል። ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ለሶስቱ የአልጀዚራ ጋዜጠኞች ፒተር ግሬትስ፣ ...

Read More »

በኦሮምያ የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለማብረድ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ተሰማሩ

ኀዳር ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት፣ የኦሮምያ ክልል ልዩ ሃይል እና የፌደራሉ አድማ ብተና ተቃውሞውን ለመቆጣጠር ባለመቻላቸውና የተቃውሞው አድማስ እየሰፋ በመሄዱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የፌደራል ዩኒፎርም ለብሰው ተቀላልቅለዋል። ለሳምንት የዘለቀው ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል እንዲሁም ከጉደር ወደ ወለጋ የሚወስዱት መንገዶች በመዘጋታቸው የትራንስፖርት አግልግሎት ለሰአታት ተቋርጧል። መልከ ጡሪ አካባቢ ...

Read More »

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) መንግስት ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ከቃል ያለፈ በተግባር እንዲያሳይ ጠየቀ

ኀዳር ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ቀንን ምክንያት በማድረግ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ከቃል ያለፈ በተግባር የተደገፈ አሰራርን እንዲከተል አሳስቧል። ሰመጉ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችን ከተቀበለች ከ68 ዓመታት በላይ እንደሆናትና መብቱ በሕገ መንግስቱ ውስጥ ቢካተትም ዜጎች ግን የሕግ ከለላው ተጠቃሚ መሆን አልቻሉም ብሎአል። እስካሁን ድረስ ...

Read More »

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በደረሰበት የቴክኒክ ችግር ምክንያት ሴኔጋል ለማረፍ ተገደደ

ኀዳር ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መነሻውን ከአዲስ አበባ በማድረግ ወደ ማሊ ባማኮ 139 መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነው አውሮፕላን አየር ላይ እያለ በአውሮፕላኑ ክንፍ ላይ በደረሰበት ድንገተኛ የቴክኒክ ብልሽት ከ45 አቂቃ በረራ በኋላ ሴኔጋል ዳካር አውሮፕላን ማረፊያ ለማረፍ ተገዷል። አውሮፕላኑ በሰላም በማረፉ በመንገደኞች ላይም ሆነ በንብረት ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አለመድረሱን ...

Read More »

በዚንባቡዌ ሶስት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በመኪና አደጋ ሕይወታቸውን አጡ

ኀዳር ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት የሚጓዙ 22 ኢትዮጵያዊያን ስደተኛችን ጭኖ ይጓዝ የነበረ አንድ ተሽከርካሪ በደረሰበት አደጋ የመኪናውን አሽከርካሪ ጨምሮ 3 ኢትዮጵያዊያን ወዲያውኑ ሕይወታቸውን ሲያጡ፣ 19 የሚሆኑት ደግሞ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የአገሪቱ የፖሊስ አዛዥ ፓውል ኒያቲ እንዳሉት የስደተኞቹን አገባብና የአደጋውን መንስኤ ፖሊስ በማጣራት ላይ መሆኑንና ጉዳተኞቹ ለሕክምና ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውን መግለጻቸውን ...

Read More »

በኦሮምያ ህዝቡ የተማሪዎችን ጥያቄ ደግፎ ወደ አደባባይ ወጣ

ኀዳር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባን አዲሱን ማስተር ፕላን በመተቸት በተማሪዎች የተጀመረው ተቃውሞ እያደገ፣ ህዝቡን በማሳተፍ በተለያዩ አካባቢዎች የቀጠለ ሲሆን ፣ የፌደራል ፖሊስ አባላት በሚወስዱት እርምጃ የታዳጊወጣቶች ህይወት ተቀጥፏል። በቦረና ዞን ዱጋዳዋ ወረዳ ፍንጭ ውሃ ከተማ ላይ ተነስቶ በነበረው ተቃውሞ ተማሪ ቢፍቶ ኮንሶ የተባለች የ10ኛ ክፍል ተማሪ ፖሊሶች የተኮሱት አስለቃሽ ጭስ አፍኗት ስትወድቅ ፣ ...

Read More »

የሰቆጣ አርሶ አደሮች እየተሰደዱ ነው

ኀዳር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የሚታየውን ከፍተኛ ረሃብ ተከትሎ መንግስት አርሶ አደሩ ቀየውን እንዳይለቅ ከፍተኛ ጥበቃ እያደረገ ቢሆንም፣ አርሶአደሮች ግን በሌሊት እየጠፉ በመሰደድ ላይ ናቸው። በፎቶ ግራፍ የተደገፉ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የሰቆታ አርሶአደሮች በቡድን በቡድን በመሆን ወደ ጎንደር የተለያዩ ከተማዎች ተሰደዋል። በሊቦ ከምከም ወረዳ በአዲስ ዘመን እና ይፋግ ከተማዎች በርካታ ስደተኞች የገቡ ሲሆን፣ የአካባቢው ነዋሪዎችም ተቀብለው ...

Read More »

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ባለፈው ግንቦት ወር ተካሂዶ በነበረው ምርጫ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቦላቸው እንደነበር አና ጎሜዝ ተናገሩ

ኀዳር ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ በአሸባሪነት የሚፈርጃቸው የአርበኞች ግንቦት7 ሊቀመንበር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ አገር ቤት ተመልሰው ግንቦት ወር ተካሂዶ በነበረው ምርጫ እንዲሳተፉ፣ በእርሳቸው በኩል መልክት እንዲያስተላልፉ ተነግሮአቸው እንደነበር የአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባል እና የኢትዮጵያ የምርጫ 97 የህብረቱ የምርጫ ታዛቢ ልኡካን መሪ ሚስ አና ጎሜዝ ተናግረዋል። ሚስ አና ጎሜዝ ይህን የተናገሩት ባለፈው ሳምንት ተዘጋጅቶ በነበረው ...

Read More »

ኢትዮጵያውያን በጋራ መታገል እንዳለባቸው ዶ/ር በያን አሰቦ ገለጹ

ኢሳት (ህዳር 27 ፣ 2008) የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር በያን አሶባ፣  ዜጎች በአንድነት ተባብረው የህዝቦችን የነጻነት ፍላጎት ከዳር እንዲያደርሱ ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ አቅርበዋል። ቀድሞ የኦነግ የአመራር አባል የነበሩት ዶ/ር በያን፣ የአገሪቷ ጉዳይ ይመለከተናል የሚሉ ግለሰቦችና ቡድኖች በመላው ኢትዮጵያ በሁሉም ማዕዘናት የነጻነት እንቅስቃሴያቸውን በጋራ ማካሄድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ተነጣጥሎ የሚደረግ አመጽና እምቢተኝነት በምንም መልኩ ሊሳካ እንደማይችል፣ ህዝቡ በጋራ ለነጻነትና ...

Read More »

በኦሮምያ የሚታየው ተቃውሞ እንደቀጠለ መሆኑን ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ኀዳር ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ ግቢያቸውን ጥለው ወጥተው የነበሩት የሁሌቦራ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ወደ ግቢያቸው ተመልሰው ከገቡ ቡዋላ እሁድ ለሰኞ አጥቢያ ሌሊቱን ተቃውሞ ሲያሰሙ አድረዋል። ዛሬ ጠዋት ፖሊሶች ወደ ግቢ በመግባት በተማሪዎች ላይ አስለቃሽ ጭስና ድብደባ በመፈጸማቸው በርካታ ተማሪዎች ተጎድተው ሆስፒታል ገብተዋል። ቲቲሲ ኮሌጅና የቴክኒክና ሙያ ተማሪዎችም እንዲሁ ዬዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ተቀላቅለው ...

Read More »