በዛሬው የአንዋር መስጊድ የጁማዓ ጸሎት ላይ የተቃውሞ ድምጾች ተሰሙ

የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ሳምንት በአንዋር መስጊድ ድንገተኛ ተቃውሞ መደረጉን ተከትሎ ፖሊስ የጸጥታ ቁጥጥሩን በማጠናከር ፍተሻዎችን ሲያካሂድ ቢያረፍድም፣ ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ግን ተቃውሞአቸውን በድምጽ ከማሰማት ያቆማቸው አልነበረም። “ኮሚቴው ይፈታ፣ መንግስት የለም ወይ” የሚሉና ሌሎችም መፈክሮች ተሰምተዋል። መንግስት የኮሚቴው አባላትን ሞራል ለመስበር የተለያዩ የፈጠራ ዜናዎችን እያሰራጨ መሆኑን ድምጻችን ይሰማ ማስታወቁ ይታወቃል።55

Read More »

በአማራ ክልል በረሃብ የተጎዱ ቤተሰቦች ቀያቸውን ለቀው እየሄዱ ነው

የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ መንግስት አመራር እስካለ ድረስ ለችግራቸው መፍትሄ እንደማያገኙም ተናግረዋል። የገዢው መንግስት ‹‹… ድርቁ ሊያስከትል የነበረውን አደጋ ተቆጣጥረናል፤ በየአከባቢው ተገቢውን እርዳታ ለተጎጂዎች እያደረስን ነው….››ቢልም ፤ በምስራቅ አማራ የትግራይ ድንበር አካበቢ የሚገኙ ተጎጅዎች ሰሞኑን እንደተናገሩት ፡- በአንድ ቀበሌ ብቻ በደረሰው ድርቅ በከፍተኛ ደረጃ የተጎዱ አምስት ሽህ ያህል ሰዎች እርዳታ ሳይደርሳቸው በችግር ላይ ይገኛሉ፡፡ ...

Read More »

በደቡብ ጎንደር የተነሳው ከባድ ጉንፋን የብዙ ሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ነው

የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በደቡብ ጎንደር ደብረታቦር አካባቢ የተነሳው ከባድ ጉንፋን ሰዎችን ለህልፈት እየዳረገ ቢሆንም የአካባቢው ባለስልጣናትም ሆኑ የክልሉ አመራሮች የወሰዱት ጠንከር ያለ እርምጃ ባለመኖሩ የአካበቢው ህብረተሰብ በጭንቀት ላይ መሆኑን ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ለየት ብሎ በተከሰተው ጉንፋን እስካሁን ስድስት ሰዎች መሞታቸው የታወቀ ሲሆን በተለይ በደብረታቦር ማረሚያ ቤት በሽታው እየተስፋፋ በመሆኑ በበሽታው የተለከፉ ሰዎችን ...

Read More »

በምእራብ አርሲ የተነሳው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው

የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በምእራብ አርሲ በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞው ተጠንከሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በዶዶላ ትናንት እና ዛሬ በነበረው ተቃውሞ ከ10 ያላነሱ ሰዎች ተገድለዋል። ሆስፒታል በርካታ ሰዎች ተመትተው የተኙ ሲሆን፣ አብዛኞቹ በህይወት የመትረፍ እድላቸው አነስተኛ ነው ተብሎአል። ትናንት በነበረው ተቃውሞ የሞቱ 2 ሰዎችን ለመቅበር የወጣው ህዝብ፣ ሟቾቹን መቅበር አትችሉም በመባሉ፣ ተቃውሞውን ጀምሯል። መብታችን ይከበር፣ የታሰሩት ...

Read More »

ለድርቅ አደጋ የተሰጠው ምላሽ ከሚጠበቀው በታችና ነው ተባለ

ኢሳት (ጥር 20 2008) አለም አቀፍ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ የድርቅ አደጋ የሰጠው ምላሽ ከሚጠበቀው በታችና አስከፊ መሆኑ አንድ አለም አቀፍ የእርዳታ ተቋም አርብ አስታወቀ። በቀጣዩ ወር ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለተጋለጡ ሰዎች 500 ሚሊዮን ዶላር ማሰባሰብ ካልተቻለም በርካታ ሰዎች ለከፋ ችግር እንደሚጋለጡ የህጻናት አድን ድርጅቱ ገልጿል። በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ በሃገሪቱ ታሪክም ሆነ በሌሎች ሃገራት ካሉት ጋር ሲነጻጸር አስከፊ ቢሆንም ዓለም ...

Read More »

በጋምቤላ ክልል በብሄር ግጭት የብዙ ሰው ህይወት ጠፋ፣ ክልሉ በፌዴራል መንግስት ቁጥጥር ስር ውሏል

ኢሳት (ጥር ፥ 20 2008) በጋምቤላ ክልል በተነሳ የብሄር ግጭት በክልሉ የትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ሃላፊን ጨምሮ ከ12 ሰዎች በላይ መገደላቸው ተሰማ። በትናንትናው ዕለት በጋምቤላ ከተማ መምህራን ኮሌጅ አካባቢ ቦምብ ፈንድቶ ባሮ ወንዝ የሚሄድ የአኝዋክ ብሄር ተወላጅ ላይ ጉዳት መድረሱን ተከትሎ በከተማዋ በአኙዋክና ኑዌር ብሄር ተወላጅ ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ግጭት ተከስቶ እንደነበረ የኢሳት ምንጮች ከስፍራው ዘግበዋል። ግጭቱን ተከትሎ የታጠቁ የክልሉ ልዩ ...

Read More »

የጋምቤላ ክልል በፊዴራል መንግስት ስር ወደቀ

በጋምቤላ ሙሉ በሙሉ በፌዴራል መንግስት ቁጥጥር ስር ወደቀች። ከአርብ ጥር 20 2008 ጀምሮ ፕሬዚደንቱን ጨምሮ የክልሉ ባለስልጣናት ከስራ ውጭ መሆናቸውን የተረጋገጠ ሲሆን፣ የክልሉንም ጸጥታ የፌዴራል መንግስት ተረክቧል። በአካባቢው የተቀሰቀሰውን የጎሳ ግጭት ተከትሎ በክልሉ ውጥረት የጨመረ ሲሆን የጋምቤላ ወህኒ ቤት ዛሬ መሰበሩ ታውቋል። በርካታ ሰዎች በዛሬው የወህኒ ቤት ጥቃት መገደላቸው ተገልጿል። የፌዴራል መንግስት የክልል ባለስልጣናትን ከስራ ውጭ ያደረገው የጸጥታን መቆጣጠር አልቻላችሁም ...

Read More »

በጋምቤላ በቀጠለው ግጭት 7 ሰዎች ተገደሉ

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል ዳይሬክተር አቶ ኒካው ኦቻላ ለኢሳት እንደገለጹት የንዌር ተወላጆች የጋምቤላ እስር ቤትን ሰብረው በመግባት 7 የአኝዋክ ተወላጆችን ሲገድሉ፣ 7ቱን ደግሞ አቁስለዋል። 4 የሌሎች ብሄረሰቦች አባላት መቁሰላቸውምን ዳይሬክትሩ ገልጸዋል። በሁለቱ ብሄረሰቦች መካካል እንዲህ አይነት ደም የሚያፋሰስ የመረረ ግጭት ተቀስቅሶ እንደማያውቅ የገለጹት አቶ ኒካው፣ ለአሁኑ ግጭት መባባስ የሪክ ማቻር ወታደሮችንና ከደቡብ ሱዳን ...

Read More »

በደቡብ ጎንደር በመቶወች የሚቆጠሩ ሰዎች ከርሃብ ጋር በተያያዘ በሽታ መሞታቸው ተሰማ

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በላይጋይንት ወረዳ ከታች ነጋላ ነዋሪዎች መካከል በቀበሌ 23፣24 እና 26 በከፍተኛ ሁኔታ በድርቅ ከመጎዳታቸው ጋር ተያይዞ በተነሳ በሽታ ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ አባዎራዎች ለሞት መዳረጋቸውን በርካቶችም የበሽታ ሰለባ ሆነው እንደሚገኙ የአካባቢው ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከ1100 በላይ የቤት እንስሳት ማለቃቸውንም አክለው ተናግረዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች ሰሞኑን እርዳታ ለመጠየቅ ...

Read More »

የመሬት መንቀጥቀጥ ሸሽተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲሄዱ የነበሩ የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የመኪና አደጋ ደረሰባቸው

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ለአስራ አምስት ቀናት ትምህርት መቋረጡን የዩንቨርሲቲው አስተዳደር መግለጹን ተከትሎ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል። በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ተጭነው ከግቢው በመውጣት ወደ ወላጆቻቸው በመሄድ ላይ ከነበሩት ተማሪዎች ውስጥ ወደ በመቂ እና ሞጆ ከተሞች መዳረሻ አካባቢ የመኪና አደጋ ደርሶባቸዋል። የአደጋው መንስኤ የሚጓዙበት ተሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ሲጓዝ ከነበረ ኤፍ ኤስ አር ...

Read More »