በኦሮሚያ ክልል መንግስት በሚወስደው እርምጃ ህዝቡ በፍርሃትና በጭንቀት ውስጥ መሆኑን ኤኤፍፒ ዘገበ

ኢሳት (የካቲት 17, 2008) በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ ዳግም ባገረሸባቸው አካባቢዎች ነዋሪዎች የፀጥታ ሃይሎች በሚወስዱት እርምጃ በፍርሃትና በጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ የአይን እማኞችን ዋቢ በማድረግ ሃሙስ ዘገበ። ለደህንነታቸው ሲሉ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉት የጊንጪ ከተማ ነዋሪዎች፣ የጸጥታ ሃይሎች በቀንና በምሽት ፍተሻን በማካሄድ ነዋሪዎች ላይ ስጋትን ፈጥረው እንደሚገኙ አስረድተዋል። ህይወታችን ትርጉም አልባ ሆኖብናል ሲሉ የገለጹት አንዲት በ40ዎቹ እድሜ ውስጥ የሚገኙ የሁለት ...

Read More »

እስራዔል በአባይ ግድብ ዙሪያ አለመግባባት ላይ በአደራዳሪነት እንድትሳተፍ መጠየቋን አንድ ጋዜጣ ዘገበ

ኢሳት (የካቲት 17, 2008) ኢትዮጵያና ግብፅ በአባይ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ያላቸውን አለመግባባት እልባት ለመስጠት እስራዔል በአደራዳሪነት እንድትሳተፍ የሃገሪቱ የፓርላማ አባላት በማግባባት ላይ መሆናቸውን የሩሳሌም ፖስት ጋዜጣ ሃሙስ ዘገበ። የሃገሪቱ የፓርላማ አባል የሆኑትና የግብፅ አል-ፋርን የቴለቪዥን ጣቢያ ባለቤት የሆኑት ቶውፊክ አካሻ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ለመምከር ካይሮ ከሚገኙት የእስራዔል አምባሳደር ቼም ኮረን ጋር ቀጠሮ መያዛቸው ተገልጿል። እስራኤል በአደራዳሪነት መሳተፏ ከፍተኛ ጠቅሜታ ያለው ...

Read More »

በኦሮምያ ተከታታይ ተቃውሞዎች እንደሚቀጥሉ ከያካባቢው የሚወጡ መረጃዎች አመልክተዋል

የካቲት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ገዢው ፓርቲ የአጋዚ ወታደሮችን በየቦታው አሰማርቶ ግድያና እስሩን አጠንክሮ ቢቀጥልም፣ በሚቀጥሉት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎችን ለማድረግ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው። በተለይ የሻኪሶ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ የጉጂ ዞን አካባቢዎች ጠንካራ ተቃውሞች እንደሚካሄዱ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በቦረና ዞንም እንዲሁ ተቃውሞዎች እንደሚቀጥሉ የአካባቢዎች ነዋሪዎች ተናግረዋል። በምእራብ ሃረርጌ ዛሬም የተቃውሞ ሰልፍ ሲካሄድ ውሎአል። ...

Read More »

ጥይት ፋብሪካው ወደ እስር ቤት ተለወጠ

የካቲት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአምቦ እና አካባቢዋ የሚካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የሚታሰሩ ወጣቶች ቁጥር በመጨመሩ፣ ከአምቦ ወጣ ብሎ የሚገኘው የጥይት ፋብሪካ ወደ እስር ቤት መለወጡን ምንጮች ገልጸዋል። በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በጥይት ፋብሪካው ግቢ ታስረው የሚገኙ ሲሆን፣ ብዙዎቹ ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተፈጽሞባቸዋል። በሌላ በኩል መንግስት የኦሮሞ የአገር ሽማግሌዎችን “በመሰብሰብ ህዝባዊ ተቃውሞው እንዲበርድ አስተዋጽኦ ...

Read More »

የኢህአዴግ መንግስት በኤርትራ ላይ ጥቃት ለመክፈት እየተዘጋጀ ነው ተባለ

የካቲት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምንጮች እንዳሉት በተለያዩ የውስጥ ችግሮች ተወጥሮ የሚገኘው ኢህአዴግ በኤርትራ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ነው። በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች በአካባቢው በሚገኙ የመንግስት ወታደሮች ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ ቆይተዋል። በርካታ ቁጥር ያላቸው ወጣቶችም እነዚህን ነጻ አውጭዎች ለመቀላቀል ድንበር አቋርጠው እየተጓዙ ነው። ይህ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ስጋት ላይ የጣለው የኢህአዴግ መንግስት፣ በኤርትራ ...

Read More »

ከወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በመንግስት ድጋፍና ቅስቀሳ የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ብዙዎችን እያስቆጣ ነው።

የካቲት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሰልፉ ጋር በተያያዘ በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ቁጣቸውን እየገለጹባቸው ካሉት ምክንያቶች መካከል አንደኛው በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በኦሮሚያ ክልል እየተፈጸመ ያለውን ግድያ ለመቃወም ባዲስ አበባና በአንዳንድ ከተሞች ለማድረግ ያቀረቡት የሰልፍ ፈቃድ ጥያቄ በተከለከለበት ሁኔታ፤ መንግስት “ወልቃይት -ትግራይ ናት” የሚል ሰልፍ በማስደረጉ ነው። ይህም በአንድ ሀገር ውስጥ ያሉ ህዝቦች በሁለት ...

Read More »

የአቶ ሃይለማርያም ዛቻም ሆነ የሃይማኖት አባቶች ተማጽኖ በኦሮምያ የሚካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ አላስቆመውም

የካቲት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአጋዚ ወታደሮች ለተቃውሞ በሚወጡት ወጣቶች ላይ በቀጥታ እንዲተኩሱ ትእዛዝ ተሰጥቷቸዋል፣አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝም መንግስታቸው የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ በአደባባይ ዝተዋል። የተለያዩ ሃይማኖቶችን የሚወክሉ የሃይማኖት አባቶች፣ በመንግስትና በህዝቡ መካከል መነጋጋር እንዲጀመር ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ሁሉ ዛቻና ምክር እየተሰጠ ቢሆንም፣ የክልሉ ወጣቶች የሚያቆመን የለም በማለት ዛሬም ትግላቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። የቦረና እና የጉጂ ዞኖች የዛሬው ...

Read More »

የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት/ኦህዲኅ/ ም/ሊቀመንበር ተፈቱ

የካቲት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ም/ል ሊቀመንበሩ አቶ ዓለማየሁ መኮንን በትናንትናው ዕለት ‹‹የፍትህ ጥያቄ የነጻነት ጥያቄ ነው›› በማለት ስለዞኑ ፍትህ መናገራቸውን ተከትሎ ታስረው ነበር፡፡ ‹‹ፍትህ በሌለበት፣ነጻነት አይኖርም ፣ነጻነት በሌለበትም ፍትህ አይኖርም ›› ብለው ተናግረዋል በሚል በዳኛ ዳዊት አድማሱ ጥሩነህ በቀረበባቸው አቤቱታ መታሰራቸው በፖሊስ የእለት መዝገብ ላይ ሰፍሮ ቢገኝም፣ ማንም ቀርቦ ስለሁኔታው ሊያስረዳ ባለመቻሉ ዛሬ ከሰዓት ...

Read More »

የእንግሊዙ ጠ/ሚኒስትር ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

የካቲት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ጠ/ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን ጉብኝቱን መቼ እንደሚያካሂዱ ባይገለጽም፣ኢትዮጵያን በሚጎበኙበት ወቅት የስደተኞች ጉዳይ ዋና አጀንዳ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። ጠ/ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን በጉብኝታቸው በእስር ላይ የሚገኙትን የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጉዳይ አንስተው ከኢህአዴግ መንግስት ባለስልጣናት ጋር ይነጋገሩ አይነጋገሩ የታወቀ ነገር የለም። ይሁን እንጅ በእንግሊዝ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተከታታይ የተቃውሞ ሰልፎችን በማካሄድ ጫና መፍጠር ከቻሉ፣ ጠ/ሚኒስትሩ ...

Read More »

በኦሮምያ የሚካሄደው ተቃውሞ ግለቱን ጨምሮ ቀጥሎአል

የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እጅግ ደም አፋሳሽ እየሆነ በመጣው የኦሮምያ ተቃውሞ፣ ህጻናት፣ ወጣቶች፣ ጎልማሶች በአጋዚ ጥይት እየተረፈረፉ ነው። በምእራብ አርሲዋ ኮፈሌ ከተማ ወደ 20 የሚጠጉ ሰዎች ሲያልቁ፣ በርካቶችም ሆስፒታል ገብተዋል። በአሳሳ ትናንት የተገደለችው የ8 አመት ህጻን የቀብር ስነስርዓት ዛሬ የተፈጸመ ሲሆን፣ የከተማው ነዋሪ መንገድ በመዝጋት ተቃውሞን ገልጿል። በምእራብ አርሲ ወደ ባሌ አቅጣጫ በሚወስደው መንገድ ላይ ...

Read More »