በአዲስ አበባ የታክሲ አሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ ጀመሩ

ኢሳት (የካቲት 21 ፥ 2008) በአዲስ አበባ ከተማ አገልግሎትን በመስጠት ላይ ይሉ በሺዎች የሚቆጠሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ተግባራዊ የተደረገን አዲስ የትራፊክ ቁጥጥር ደንብ በመቃወም ሰኞ የስራ ማቆም አድማ ጀመሩ። የታክሲ አሽከርካሪዎች የወሰዱትን እርምጃ ተከትሎም የከተማዋ ነዋሪዎች የዕለት ከእለት የኑሮ እንቅስቃሴያቸው መስተጓጎሉን እማኞች ገልጸዋል። ከአራት አመት በፊት የወጣውና ከቀናት በፊት ተግባራዊ መደረግ የጀመረው የትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ለስራ አስቸጋሪ በመሆኑ ደንቡ መሻሻል እንዳለበት ...

Read More »

በአዲስ አበባ የሚካሄደው የታክሲ አሽከርካሪዎች አድማ እንደቀጠለ ነው

የካቲት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን አሽከርካሪዎች ጥፋት ሲያጠፉ ፈቃዳቸውን እስከመሰረዝ የሚያደርሰውን ከበድ ያለ ቅጣት የያዘውን ህገደንብ በመቃወም በአ/አ ከተማ የተጀመረው የታክሲ ማቆም አድማ የቀጠለ ሲሆን ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ታክሲ በመጠበቅ ላይ የነበረው ህዝብ ሆን ብሎ መንገዶችን በመዝጋት፣ ሌሎች የግል፣የንግድና የመንግስት ተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ እንዲታወክ በማድረግ ተቃውሞውን ተቀላቅሏል። ተቃውሞውን ተከትሎ የመንገድና ትራንስፖርት ባለስልጣን ደንቡ ...

Read More »

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በታክሲዎች አድማ ምክንያት ተሰረዘ

የካቲት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት 120ኛውን የአድዋ ድል በዓል በነገው እለት ለማካሄድ የያዘውን የፖናል ውይይት ከአ/አ ታክሲዎች አመጽ ጋር በተያያዘ ለመሰረዝ ተገዷል። ጽ/ቤቱ የካቲት 22 ቀን 2008 ዓ.ም በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል የፖናል ውይይቱን ለማካሄድ አቅዶ ለሆቴሉ ክፍያ የፈጸመውና ለተሳታፊዎች ጥሪ ያስተላለፈው ከሳምንት በፊት ነበር። ሆኖም በአ/አ ከተማ በመካሄድ ...

Read More »

የጋይንት ህዝብ ስለወልቃይት ጉዳይ አትጠይቅም በመባሉ ስብሰባ ረግጦ ወጣ

የካቲት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ጎንደር ዞን በጋይንት ከተማ የክልሉ ባለስልጣናት ህዝቡን ለማወያየት ትናንት እሁድ የጠሩት ስብሰባ፣ በተቃውሞ ተበትኗል። የተቃውሞው መነሻ ደግሞ ከወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ፣ ህዝቡ ጥያቄ ማቅረብ በመጀመሩና ስብሰባውን የሚመራው ጋዜጠኛ ” ስለወረዳችሁ እንጅ ስለሌሎች አካባቢዎች ጥያቄ መጠየቅ አትችሉም” ማለቱን ተከትሎ ነው። ስብሰባው የተጠራው ከዚህ ቀደም የከተማዋ ነዋሪዎች የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ...

Read More »

ኤርትራ – ከኢትዮጵያ መንግስት የተሰነዘረባት ክስ ፈጽሞ ውሸት እንደሆነና የኢትዮጵያ መንግስት ከውስጥ የተነሳበትን ህዝባዊ ተቃውሞ ለማድበስበስ የፈበረከው መሆኑን አስታወቀች።

የካቲት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ፦” ውሸት ቢደጋገምም፤ እውነትን ሊቀብር አይችልም” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ የህወሀት አገዛዝ እንደተለመደው ኤርትራን ለማጠልሸት ኋላ ቀርና ርካሽ ፕሮፓጋንዳ መንዛቱን በመጥቀስ፤ የዚህ ፕሮፓጋንዳ ዓላማውም እውነታውን ለመደበቅና ከውስጥ እያየለ የመጣበትን ህዝባዊ ተቃውሞ ውጫዊ ለማስመሰል እንደሆነ ገልጿል። የኤርትራ ህዝብና መንግስት የዚህ ዓይነት ተደጋጋሚ የውሸት ፕሮፓጋንዳ እየተነዛባቸው ባለበትና መሬታቸው በኃይል በተያዘበት ...

Read More »

አርበኞች ግንቦት በበርን ስዊዘርላንድ የተሳካ ህዝባዊ ውይይት አደረገ

የካቲት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የንቅናቄው አመራር የሆኑት አርበኛ ኤፍሬም ማዴቦ፣ ጋዜጠኛ አፈወርቅ አግደው ፣ የኢሳት ቴሌቪዥንና ሬዲዮ የጀርመን ሃገር ቃል አቀባይ ሃይሉ ማሞ፥ ተቀማጭነታቸው በስዊዘርላንድ የሆኑ የሃይማኖት አባቶችና ከተለያዩ የስዊዘርላንድ ከተሞችና ከሙኒክ ጀርመን ከተማ በመጡ ሃገርወዳድ ኢትዮጵያውያን በታደሙበት በዚህ ታላቅ ህዝባዊ ውይይት ላይ የወቅቱ የሃገራችን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ሁኔታ፣ የአርበኞች ግንቦት 7 የትግል እንቅስቃሴ ፣ ላለፉት ...

Read More »

ፍል ውሃ አካባቢ በሚገኘው ተውፊቅ መስጊድ ተቃውሞ ተካሄደ

ኢሳት (የካቲት 18 ፥2008) በእስር ላይ የሚገኙ የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እንዲፈቱና በሃገሪቱ ያለን ጭቆና እንዲቆም የሚጠይቅ ተቃውሞ አርብ ፍል ውሃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው ተውፊቅ መስጊድ ተካሄደ። የአርብ ልዩ የጾም (ጁምዓ) ስነ-ስርዓት ተከትሎ በተካሄደው በዚሁ ተቃውሞ የሙስሊም ማህበረሰብ መፈክሮች የተጻፉባቸው ፊኛዎችን ወደሰማይ መልቀቃቸውን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል። ባለፉት ሁለት ሳምንታት በድምፅና ድምፅ አልባ የሆኑ ተቃውሞዎች በአንዋር መስጊድ ...

Read More »

ቤተ-እስራዔላውያንን ለማጓጓዝ የወጣው እቅድ እንዲዘገይ ተደረገ

ኢሳት (የካቲት 18 ፥2008) በቅርቡ የመጨረሻዎቹ ዘጠኝ ሺህ ቤተ-እስራዔላውያን ከኢትዮጵያ ወደእስራዔል ለማጓጓዝ ቃል ገብታ የነበረችው እስራዔል እቅዱ እንዲዘገይ ማድረጓን አርብ ይፋ አደረገች። የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ እቅዱ ከበጀት ጋር በተያያዘ እንደዘገይ መደረጉን ቢገልፅም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች አካላት ድርጊቱ በእስራዔል ጥያቄን አስነስቶ ካለው ከዘረኝነት ጉዳይ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ገልጸዋል። የእስራዔል ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጄኔራል ዳይሬክተር የሆኑት ኤሊ-ግሮነር እቅዱ ከመነሻውም በጀት ሳይያዝለት ...

Read More »

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ኖርዌይ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ተገዢ እንድትሆን ጠየቀ

ኢሳት (የካቲት 18 ፥2008) የኖርዌይ መንግስት በመቶዎቹ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ያለፍላጎታቸው ወደሃገራቸው ለመመለስ የያዘውን እቅድ ተከትሎ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሃገሪቱ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ተገዢ እንድትሆን አሳሰበ። ሃገሪቱ በስደተኞች ላይ እየያዘች የመጣችውን አዳዲስ አቋሞች የተቸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ኖርዌይ ለአለም አቀፍ ህግጋት ተገዢ ያለመሆን አቅጣጫ እየተከተለች እንደሆነም አስታውቋል። ኖርዌይ ተግባራዊ ለማድረግ ያሰበችውን የስደተኞች አዲስ እቅድ ምክንያት በማድረግ የሃገሪቱ ባለስልጣናት ከ500 የሚበልጡ ...

Read More »

ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ካለው ተቃውሞ ጀርባ የኤርትራ እጅ አለበት ሲል ከሰሰ

ኢሳት (የካቲት 18 ፥2008) የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ካለው ተቃውሞ ጀርባ የኤርትራ እጅ አለበት ሲሉ አዲስ ተቃውሞ ማቅረባቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ አርብ ዘገበ። መነሻውን ከጎረቤት ኤርትራ ያደረጉ አካላት በተቃውሞ ስለመሳተፋቸውንና ችግሩን በማባባስ ላይ ስለመሆናቸው በቂ ማስረጃ አለን ሲሉ የመንግስት ቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ረዳ ለዜና አውታሩ ገልጸዋል። የመንግስት ባለስልጣናት በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ላለው ተቃውሞ በክልሉ የመልካም አስተዳደር ተግባራዊ አለመደረጉ ...

Read More »