አፍሪካ ቫኬሽን የመዝናና ሆቴል ከባድ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደረሰበት

ኢሳት (የካቲት 22 ፥ 2008) በደቡብ ክልል ሃዋሳ ከተማ ላንጋኖ ሃይቅ ዳርቻ የተገነባውና የባለ አምስት ኮከብ ደረጃ ያለው አፍሪካ ቫኬሽን የመዝናኛ ሆቴል ሰኞ ምሽት ከባድ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደረሰበት። ምክንያቱ ባልታወቀው በዚሁ የእሳት ቃጠሉ የሆቴሉ የማረፊያና ሌሎች ክፍሎች ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው እማኞች ዋቢ በማድረግ በሃገር ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በዚሁ የመዝናኛ ሆቴል ላይ በአጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ለማወቅ የተደረገ ጥረት ...

Read More »

በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ በተለያዩ ከተሞች መካሄዱን አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ

ኢሳት (የካቲት 22 ፥ 2008) በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውና ሶስተኛ ወሩን ያስቆጠረው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተቃውሞ በተያዘው ሳምንት በተለያዩ የክልሉ ከተሞች መቀጠሉን አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ማክሰኞ ዘገቡ። የመንግስት ባለስልጣናት ተቃውሞን ለመቆጣጠር እርምጃን እንደሚወስዱ በተደጋጋሚ ቢያሳስቡም ይኸው ተቃውሞ በምስራቅና በምዕራብ ሃረርጌ አካባቢዎች እልባት አለመገኘቱ ታውቋል። የአዲስ አበባ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኙ ከተሞች ሳይቀር በወታደራዊ ተሽከርካሪዎች እየጠበቁ እንደሚገኝ አፍሪካ ታይምስ ...

Read More »

ለሁለት ቀናት የተጠራው የአዲስ አበባ ታክሲ አሽከርካሪዎች አድማ ወደ ኦሮምያ ተዛመተ

የካቲት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት የተጠራው የታክሲ አሽከርካሪዎች አድማ ለሁለተኛ ቀን ከቀጠለ በሁዋላ፣ ከሰዓት በሁዋላ በተለይም ከቀኑ 10 ሰአት ጀምሮ ታክሲዎች ቀስ በቀስ ስራ ጀምረዋል።በአዲስአበባ የተደረገውን አድማ ተከትሎ፣በኦሮምያ የተለያዩ ከተሞችም ተመሳሳይ የስራ ማቆም አድማ ተደርጓል።በሆለታ፣ ቡራዩ፣ግንጪ፣ አምቦ፣ ወሊሶና አካባቢዋ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ ውሎአል። በአዲስ አበባ ጠዋት አካባቢ ጥቂት ታክሲዎች ስራ ለመጀመር ...

Read More »

አቶ በከር ሻሌ የኦህዴድ ጽ/ቤት ሃላፊ ሆነው ተሾሙ

የካቲት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእስር ላይ የሚገኙትን አቶ መላኩ ፋንታን በመተካት የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ከሶስት አመታት በፊት የተሾሙት አቶ በከር ሻሌ ፣ ከዛሬ ጀምሬ የኦህዴድ ድርጅት ጽ/ቤት ሃላፊ ሆነው መሾማቸውን ፎርቹን ዘግቧል።በኦሮምያ በመካሄድ ላይ ያለውን ተቃውሞ ተከትሎ ፣ አቶ በከር የክልሉን ፕሬዚዳንት አቶ ሙክታር ከድርን ይተካሉ ተብሎ በስፋት ሲወራ ቆይቷል። ይሁን ...

Read More »

በዲላ፣ ሱሉሉታና አዳማ ከተሞች ከፍተኛ የሆነ የውሃ ችግር ተከሰተ

የካቲት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በዲላ ከተማ በተፈጠረው ከፍተኛ የሆነ የውሃ ችግር ነዋሪዎች ፣ቢጫ ጀሪካኖቻቸውን አሰልፈው ወንዝ እየወረዱ ለመቅዳት ተገደዋል። ከዚህ ቀደም በ15 ቀን አንድ ቀን ይገኝ የነበረው የቧንቧ ውሃ አሁን በወር አንድ ቀን ለማግኘት እየቸገረ መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። በሱሉልታም እንዲሁ ውሃ ከጠፋ ወራት በመቆጠራቸው ህዝቡ የቆሸሸና የተበከለ ውሃ ለመጠቀም መገደዱን የአካባቢው ምንጮች በቪዲዮ አስደግፈው ...

Read More »

ዘጠኝ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የድራግ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ ተገለጸ።

የካቲት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ጸረ- ድራግ ኤጀንሲ ጀነራል ሴክሬታሪን ጠቅሶ ዘጋርዲያን እንደዘገበው ምርመራ እየተደረገባቸው ካሉት ዘጠኝ አትሌቶች መካከል አምስቱ ታዋቂና ስመ-ጥር አትሌቶች ናቸው። ሴክሬታሪው አቶ ሰሎሞን መአዛ ለአሶሲየትድ ፕሬስ እንደተናገሩት ታዋቂዎቹ አምስት አትሌቶች አስደናቂ ድል አስመዝግበው መመለቸውን ተከትሎ አበረታች መድሀኒት ወስደዋል የሚል ቅድመ-ምርመራ ውጤት በመደረጉ ነው በኤጄንሲው ምርመራ እየተደረገባቸው ያለው። ይሁንና ጀነራል ሴክሬታሪው ...

Read More »

በክልሎች ህዝብ ማመላለሻ አገልግሎት ሰጪዎች በአዲስ አበባ የተቀሰቀሰውን የስራ ማቆም አድማ ተቀላቀሉ

ኢሳት (የካቲት 21 ፥ 2008) የህዝብ ማመላለሻ አገልግሎቶችን በክልል የሚሰጡ አውቶቡሶች በአዲስ አበባ የተቀሰቀሰውን የስራ ማቆም ተቃውሞውን ሰኞ እንደተቀላቀሉት ታውቋል። በአሰላ፣ ባሌ፣ እና ሮቤ ከተሞች የተጀመረው የትራስፖርት ማቆም አድማ ተከትሎም በየከተሞቹ የትራንስፖርት እጥረት መከሰቱን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስራ ማቆም አድማ ላይ ያሉ ታክሲዎች አገልግሎታቸውን እንዲጀምሩ ጥሪን ቢያቀርቡም የታክሲ ማቆም አድማው ሰኞ ምሽትም መስተዋሉን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

Read More »

በሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ህዝባዊ እምቢንተኝነቱ ቀጥሏል

ኢሳት (የካቲት 21 ፥ 2008) በሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ለሁለተኛ ቀን ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ቀጥሎ መዋሉን እሳት ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጹ። ተቃውሞው ከተቀሰቀሰ በኋላ በወረዳዋ ባለስጣናት መካከል ውዝግብ መፈጠሩም ከውስጥ ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ተከትሎ የዳባት ወረዳ የደህንነት ሃላፊ፣ የሚሊሺያ ዘርፍ ሃላፊና፣ የሲቪል ሰርቪስ መስሪያ ቤት ሃላፊ መታሰራቸውን ከስፍራው የተገኘው መረጃ አመልክቷል። በዛሬው ምሽት ከሌሎች ከተሞች ጋር የሚያገናኙ መንገደችም ...

Read More »

የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ዋጋ የቀነሰ ቢሆንም መንግስት ተገቢውን ቅናሽ አለማድረጉ ቅሬታን ቀሰቀሰ

ኢሳት (የካቲት 21 ፥ 2008) በአለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ዋጋ የቀነሰ ቢሆንም መንግስት ተገቢውን ቅናሽ አላደረገም በሚል የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታን አቀረቡ። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት በበኩላቸው በአለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ ካልፈው አመት ጀምሮ የ40 በመቶ ቅናሽን ቢያሳይም መንግስት ተግባራዊ ያደረገው ቅናሽ ከ12 በመቶ እንደማይበልጥ መግለጻቸውን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል። የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ስራ ...

Read More »

ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት አነስተኛ ነው ተባለ

ኢሳት (የካቲት 21 ፥ 2008) በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ የተጋለጡ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት አነስተኛ መሆኑን እንዳሳሰበው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰኞ ገለጠ። ለተረጂዎች እየቀረበ ያለው እርዳታ በማለቅ ላይ ቢሆንም ተተኪ የእርዳታ አቅርቦትን ለማድረስ እየተደረገ ያለው ጥረት ግን እጅግ ዝቅተኛ መሆኑን ድርጅቱ በአፅንዖት አስታውቋል። አለም አቀፍ የምግብ እርዳታን ወደሃገር ውስጥ ለማስገባት በትንሹ የሶስት ወር ጊዜን የሚወስድ ሲሆን እርዳታው ...

Read More »