.የኢሳት አማርኛ ዜና

ለሃይማኖታዊ የሃጂ ፀሎት የሚጓዙ ምእመናን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ መንገላታት ደረሰባቸው።

ለሃይማኖታዊ የሃጂ ፀሎት የሚጓዙ ምእመናን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ መንገላታት ደረሰባቸው። ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 08 ቀን 2010 ዓ/ም ) መነሻቸውን ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ በማድረግ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተገቢውን የበረራ መስፈርቶችን አሟልተው ወደ ሳኡዲ አረቢያ ለመብረር ሲጠባበቁ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጣቸው በረራቸው እንዲሰረዝ በመደረጉ ለከፍተኛ እንግልትና ለተጨማሪ ወጪዎች ተጋላጭ ሆነዋል። አብዛሃኞቹ እድሜያቸው የገፋ አቅመ ደካማ አዛውንቶች፣ ...

Read More »

የዓባይ ግድብን እየሠራ የነበረው ሳሊኒ የኮንስትራክሽን ኩባንያ መንግስትን ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ካሳ መጠየቁ ተሰማ።

የዓባይ ግድብን እየሠራ የነበረው ሳሊኒ የኮንስትራክሽን ኩባንያ መንግስትን ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ካሳ መጠየቁ ተሰማ። ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 08 ቀን 2010 ዓ/ም ) የዓባይ ግድብን የሜካኒካል ስራ ኃላፊነት የወሰደው የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን በምህጻረ ቃሉ ሜቴክ፣ በኮንትራት የወሰደውን ሥራ በተቀመጠለት ጊዜ እና በትክክል ሰርቶ ማስረከብ ባለመቻሉ የጣሊያኑ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ሌሎች ስራዎችን መቀጠል አልቻለም ሲሉ ምንጮች ጠቁመዋል። በዚህም ምክንያት ውሉ ያልተጠበቀለት ...

Read More »

በጅግጅጋ የሶማሊያ ሪፐብሊክ ባንዲራና መገንጠልን የሚቀሰቅሱ ባነሮች በብዛት እየታተሙ መሆናቸው ተገለጸ። ኮማንድ ፖስቱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

በጅግጅጋ የሶማሊያ ሪፐብሊክ ባንዲራና መገንጠልን የሚቀሰቅሱ ባነሮች በብዛት እየታተሙ መሆናቸው ተገለጸ። ኮማንድ ፖስቱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 08 ቀን 2010 ዓ/ም ) በስፍራው ያሉ የኢሳት ወኪሎች ባደረሱን መረጃ መሰረት፣ ቀደም ሲል አብዲ ኢሌ ያደራጃቸው ሄጎ የእተባሉ የሚጠሩት ቡድኖች፤ ትናንትና በጅግጅጋ ከተማ የመንግስት መኪኖችን ጭምር በመጠቀም እና የኦብነግን ባንዲራ በማውለብለብ ብጥብጥ ለመፍጠር ሞክረዋል። እነዚሁ ቡድኖች ክልሉን ለማረጋጋት ከተሰማራው የመከላከያ ...

Read More »

የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን አዲስ የዋጋ ታሪፍ ጭማሪ ማስተካከያ ለማድረግ መወሰኑን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን አዲስ የዋጋ ታሪፍ ጭማሪ ማስተካከያ ለማድረግ መወሰኑን አስታወቀ። ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 08 ቀን 2010 ዓ/ም ) የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን ተጨማሪ የዋጋ ታሪፍ ሊጥል ነው። ከፍተኛ የኤሌትሪክ ፍጆታ ተጠቃሚዎች በአዲሱ ተመን እስከ 350 በመቶ ጭማሪ ክፍያ ይጠየቃሉ። ድርጅቱ እዚህ ውሳኔ ላይ ከመድረሱ አስቀድሞ ከኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት (EEU)፣ ከኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ፓወር (EEP)፤ ከውሃ፣ መስኖ እና ኤሌትሪክ ...

Read More »

አቶ ተስፋዬ ኡርጌ እየተካሄዱ ካሉ ግጭቶች ጋር በተያያዘ ምርመራ ተጀመረባቸው

(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 9/2010) የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ባለስልጣን የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ካሉ ግጭቶች ጋር በተያያዘም ምርመራ እንደተጀመረባቸው ተገለጸ። አቶ ተስፋዬ ኡርጌ የሰኔ 16ቱን የቦምብ ጥቃት በማስተባበር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል። ግለሰቡ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ የግዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ወደ ወህኒ ቤት ተመልሰዋል። ተጠርጣሪው አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በውጭ ሃገር ካሉ ቡድኖች ጋር አላቸው በሚል የተጀመረባቸው ምርመራም መቀጠሉ ...

Read More »

ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳና ሌሎች የፖሊስ አመራሮች ዋስትና ተፈቀደ

 (ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 8/2010)በመስቀል አደባባይ ሰኔ 16 በደረሰው የቦንብ ፍንዳታ የአሰራር ክፍተት አሳይተዋል ተብለው ታስረው የነበሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ ጨምሮ 11 የፖሊስ አመራሮችም ዋስትና ተፈቀደላቸው። አቃቤ ህግ የፖሊስ አመራሮቹ  በዋስ ቢለቀቁ እንደማይቃወም ለፍርድቤቱ ገልጾ ነበር። የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ በ15 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፈቅዷል። ኮማንደር ገብረኪዳን አስገዶም፣ ኮማንደር ...

Read More »

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ሃገሩ እንዲመለስ ተጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 8/2010)የመብት ተሟጋቹ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ሃገሩ እንዲመለስ ጥሪ ቀረበ ። ለዚህ ታዋቂ አትሌት የጀግና አቀባበል ለማድረግ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዝግጅት ማድረጋቸውን ባወጡት የጋራ መግለጫ አስታውቀዋል። በነሃሴ 2008 ዓም በብራዚል ሪዮ ዲጄነሮ በተካሄደው ኦሎምፒክ በማራቶን ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘው  አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ  ውድድሩን ማሸነፉ ይታወሳል። በዚሁ ወቅትም ሩጫውን ሲያጠናቅቅ በኢትዮጲያ የሚካሄዱ ግድያዎችን በአጠቃላይ የመብት ...

Read More »

ሱልጣን ሃንፍሬ አሊሚራህ ከስደት ተመለሱ

(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 8/2010)  የአፋር መንፈሳዊ መሪ ሱልጣን ሃንፍሬ አሊሚራህ ከስደት ተመለሱ።በከሱልጣን ሃንፍሬ አሊሚራህ ጋር የአፋር ሕዝብ ፓርቲ መሪ ዶ/ር  ኮንቴ ሙሳ እንዲሁም የአፋር ሰብዓዊ መብት ድርጅት ሊቀመንበር አቶ ጋአስ አህመድም  በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ገብተዋል። በተመሳሳይ ዜና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አመራሮችም ዛሬ  ወደ  ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። ከአምስት አመታት በፊት የሱልጣን አሊ ሚራህን ማለፍ ተከትሎ፣ የሱልጣን ማዕረጉን የወረሱትና ባዕለ-ሲመታቸውን በአፋር ክልል በአሳይታ   ከተማ  ያካሄዱት ...

Read More »

አርበኞች ግንቦት ሰባት አቀባበል ዝግጅቱ እየተጠናቀቀ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 8/2010) አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ወደ ሀገር ቤት በሚገባበት ሁኔታ ላይ የአቀባበል ኮሚቴው ዛሬ መግለጫ ሰጠ። ኮሚቴው ከዛሬ ጀምሮ የአቀባበል መርሃግብሩን የተመለከቱ ስራዎችን በይፋ መጀመሩን አስታውቋል። ናፍቆት የሚል መጠሪያ የተሰጠው የአቀባበል ስነስርዓት ላይ ኢትዮጵያውያን በመሳተፍ ለንቅናቄው መሪዎችና አባላት ደማቅ አቀባበል እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል። በሌላ በኩል በእስር የሚገኙና በአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ስም የተከሰሱ 53 ሰዎች ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ...

Read More »

በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከጅቡቲ እየወጡ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 8/2010) በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን  በየዕለቱ ከጅቡቲ በመውጣት ወደ ሀገር ቤት እየገቡ መሆናቸው ተገለጸ። በምስራቅ ኢትዮጵያ ከተፈጠረው ግጭት ጋር በተያያዘ  የሚደርሰውን ጥቃት በመፍራት በርካታ ኢትዮጵያውያን ጅቡቲን ለቀው መውጣታቸውን ቀጥለዋል። በድሬዳዋ አምስት የጅቡቲ ዜጎች ባለፈው ሳምንት መገደላቸውን ተከትሎ በጅቡቲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጥቃት እየተፈጸምብን ነው ሲሉ ለኢሳት ገልጸዋል። ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከጅቡቲ ተፈናቅለው በምስራቅ ኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች ...

Read More »