.የኢሳት አማርኛ ዜና

በብዙ መቶሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ዋሉ

የካቲት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-<<ጅሀዳዊ ሀረካት>> የተሰኘውንና በ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሰሞኑን የተላለፈውን ፊልም በመቃወምና ለታሰሩት የሙስሊም መፍትሔ =  አፈላ ላጊ ኮሚቴዎች አጋርነታቸውን ለመግለጽ በብዙ መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ዛሬ ከፍተኛ ተቃውሞ ሲያሰሙ ውለዋል። “መሪዎቻችን ይፈቱ! ዓላማችን ኢስላማዊ መንግስት ሳይሆን የሀይማኖት ነፃነታችንን ማግኘት ነው! ድምፃችን ይሰማ ፣ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ይቁም>>የሚሉ እንዲሁም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን የሚያወግዙ መፈክሮች ...

Read More »

የኢህአዴግ መንግስት በሳኡዲ አረቢያ-ሪያድ ለ ዓባይ ግድብ ቦንድ ግዥ የጠራው ስብሰባ ወደ ከፍተኛ ተቃውሞ ተቀይሮ በተቃውሞ ተጠናቀቀ

የካቲት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ለ አባይ ግድብ ማሰሪያ የሚውል የቦንድ ግዥ የሚካሄድበትን ፕሮግራም የያዘው ከሳምንታት በፊት ነው። በፕሮግራሙ መሰረት ትናንት ሐሙስ ከወትሮው በተለዬ መልኩ በሪያድና አካባቢው የሞኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በስፍራው በመገኘት የኮሙኒቲውን አዳራሽ ከ አፍ እስከ ገደፉ ይሞሉታል። የቦንድ ግዥውን ፕሮግራም ለመምራት ወደዚያው ያቀኑት የኢህአዴግ ባለስልጣናትም  በስብሰባው ከተገኘው በርካታ ሰውደጎስ ያለ ገንዘብ ...

Read More »

በሳውዲ የሚኖሩ በርካታ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን ታሰሩ

የካቲት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያውያኑ ዘወትር  አርብ እየተሰባሰቡ የሚያደርጉትን የአምልኮ መርሀግብር ሲጀምሩ የሳውዲ የጸጥታ ሀይሎች ወደ አምልኮ ስፍራው በመሄድ አፍሰው ወስደዋቸዋል። 43 ሴቶች እና 6 ወንዶች መታሰራቸውን በሳውዲ ነዋሪ የሆኑት የእምነቱ ተከታይ  አቶ በሪሁን አሰፋ ገልጸዋል ፤ ሶስቱ አገልጋዮች ለብቻ ተወስደው =መታሰራቸውን አክለዋል። የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውን ሰዎች ወደ አገራቸው ሊመልሱዋቸው እንደሚችሉ የገለጡት አቶ በሪሁን፣ የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ...

Read More »

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና የፍትህ አሳተሚ ጥፋተኞች ተባሉ

የካቲት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 16ኛ ወንጀል ችሎት በፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና በአሳታሚው ድርጅት በማስተዋል የህትመትና የማስታወቂያ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ በአቶ ማስ  ተዋል ብርሀኑ ላይ የጥፋተኝነት ብይን ሰጥቷል። የችሎቱ ዳኛ አቶ አይሸሹ ሽመልስ ውሳኔያቸውን በንባብ ያሰሙ ሲሆን የፌደራል አቃቢ ህግ ያቀረባቸውን 4 ክሶች በንባብ በማሰማት ፣ ሙሉ ...

Read More »

ከ10 አመታት በላይ ጊዚያቸው ያለፈባቸው መድሀኒቶች በመጋዘን ውስጥ ተገኙ

የካቲት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር እንዳስታወቀው ጊዜያቸው ያለፈባቸው በአማካኝ ከ8 እስከ 14 አመታት የቆዩ መድሀኒቶች በከነማ ፋርማሲዎች ተከማችተው ተገኝተዋል። የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ፋና እንዳስደመጠው መድሀኒቶቹ በህገወጥ መልኩ እየወጡ ለፋርማሲዎች ሳይሸጡ አልቀረም። የአዲስ አበባ የጤና ቢሮ እንዳስታወቀው መድሀኒቶቹ የተጠራቀሙት የኦዲት ምርመራ ስላልተደረገባቸው ነው የሚል መልስ ሰጥተዋል። በመንግስት ፋርማሲዎች ተከማችተው የሚገኙ ጊዜያቸው ያለፈባቸውን መድሀኒቶች አንዳንድ ...

Read More »

የጅማ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ተቃውሞአቸውን ገለጹ

ጥር ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ ተማሪዎች ለኢሳት እንደገለጡት ቁጥራቸው ከ500 የማያንስ ሙስሊም የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች በስታደየም አካባቢ በመሰባሰብ     ጥያቄያቸው መልስ እንዲያገኝ ጠይቀዋል።  በደህንነት ሀይሎች ታፍነው የተወሰዱት ተማሪዎች ያሉበትን ሁኔታ ዩኒቨርስቲው  እንዲያሳውቃቸው ተማሪዎች ጥያቄ አቅርበዋል። የዩኒቨርስቲው ባለስልጣናት ዲኑ ለስብሰባ ከአካባቢው በመራቃቸው መልስ ሊሰጡዋቸው እንደማይችሉ ለተማሪዎች ቢነግሩም፣ ተማሪዎቹ ግን በተቃውሞአቸው ገፍተውበታል። ይህን ዜና እስካጠናከርንበት በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር እስከ ...

Read More »

የምርጫ ምዝገባ መጠናቀቁ በይፋ ከተገለጠ በሁዋላ ምዝገባው ዛሬም ቀጥሎአል

ጥር ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባለፈው ሳምንት የምርጫ ምዝገባው 100 በመቶ የተሳካ በመሆኑ ምርጫውን ከሁለት ቀናት የበለጠ እንደማያርዝም ገልጾ ነበር። ኢሳት ለምርጫው ተገዶም ቢሆን የተመዘገበው ህዝብ ከ30 በመቶ እንደማይበልጥ የምርጫ ቦርድ የውስጥ ምንጮችን በመግልጽ ዘግቧል። ከፍተኛ የኢህአዴግ ካድሬዎች ለወረዳ አመራሮች ቀይ መብራት በርቶባችሁዋል በማለት ማስፈራራታቸውን ተከትሎ ፣ አመራሩ ወደ ህዝቡ በመውረድ በእየቤቱ ሲያስገድዱ ቆይተዋል። ባለፈው ...

Read More »

ግንቦት 7 ጅሐዳዊ ሐረካት ተብሎ የተዘጋጀውን ፊልም አወገዘ

ጥር ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ግንቦት ሰባት የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለኢሳት በላከው መግለጫ ጅሃዳዊሐረካት የተባለው ድራማ ሁለቱን ትልልቅና ጥንታዊ የኢትዮጵያ ሐይማኖቶች ለማጣላት ሆን ተብሎ የተሰራ ነው ብሎአል። ኢትዮጵያ እስልምናንም ሆነ ክርስትናን በቅድምያ ከተቀበሉ አገሮች አንዷ መሆኗ ብቻ ሳይሆን ክርስትናና እስልምና ከአንድ ሺ አመታት በላይ በሠላም ተከባብረዉ ጎን ለጎን የኖሩባት ብቸኛ አገር መሆኑዋን የገለጠው ግንባሩ፣ የአገር አንድነትና የህዝብ ...

Read More »

በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ ሶስት ሰዎች ሞቱ

ጥር ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በወረዳ 10 በተለምዶ ሰራተኛ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ47 አባዎራዎች መኖሪያ ቤቶችና አራት ተሽከርካሪዎች በአደጋው ምክንያት የወደሙ ሲሆን ሶስት ሰዎችም በአደጋው ምክንያት መሞታቸው ታውቋል። እሳቱን ለማጥፋት በስፍራው በነበሩ የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ኤጀንሲ 2 ሰራተኞችና 4 የግቢው ነዋሪዎች ላይ ደግሞ የቃጠሎ አደጋ ደርሷል። የኤጀንሲው የኮሚዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ ንጋቱ ማሞ እንዳሉት ...

Read More »

አንድነት ፓርቲ ጀሃዳዊ ሀረካትን አጣጣለው

ጥር ፳፱ (ሀያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ፓርቲው ” በ‹‹ጀሃዳዊ ሃረካት›› ትረካ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ጥያቄ ማዳፈን አይቻልም!” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ፣ በገዢው ፓርቲ ድርጊት ማፈሩንና ማዘኑን ገልጿል። ገዥው ፓርቲ  ዜጎች በማንኛውም መንገድ የሚያነሱትን ጥያቄ በግልጽና በውይይት መፍታት ያለመፈለጉ ግልጽ ሀገራዊ አደጋ እየሆነ መምጣቱ እየታየው ነው የሚለው አንድነት፣ “ኢትዮጵያን የምታክል ትልቅ ሀገር እያስተዳደረ ባለ መንግሥት” ማዘኑንም አልሸሸገም። አንድነት በኢትዮጵያ ሕዝብ ...

Read More »