.የኢሳት አማርኛ ዜና

የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ የቀድሞ አመራሮቹን እያሳተፈ ነው ተባለ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 3/2010) በኢትዮጵያ የተከሰተው ቀውስ ተባብሶ በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት ስብሰባ የተቀመጠው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ የቀድሞ አመራሮቹን ማሳተፉ ታወቀ። በቅርቡ በሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ላይ የተጀመረውና በኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ላይም የቀጠለው የቀድሞ አመራሮችን የማሳተፍ ርምጃ በመተካካት ስም ከሂደቱ የወጡትን ይበልጥ ተዋናይ እያደረጋቸው መምጣቱም ተመልክቷል። በስብሰባው ማጠቃለያ የካቢኔ ብወዛ እንደሚኖርም ይጠበቃል። የሕወሃት ደጋፊዎች በበኩላቸው አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ እንዲለቁ በመጠየቅ ...

Read More »

በመላው አለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አደባባይ በመውጣት ድምጻቸውን አሰሙ

(ኢሳት ዜና –ታህሳስ 3/2010) በሊቢያ በጥቁር አፍሪካውያን በተለይም በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ያለው የባሪያ ንግድ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መቆም አለበት ሲሉ በመላው አለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አደባባይ በመውጣት ድምጻቸውን አሰሙ። በግሎባል አሊያንስና በሌሎች ሲቪክ ድርጅቶች አስተባባሪነት በተካሄደው በዚህ ሰልፍ ለኢትዮጵያውያኑ ስደትም ሆነ እንግልት ዋናው ተጠያቂ ህዝብን በመከፋፈል የሚታወቀው የህወሃት አገዛዝ ነው ሲሉ ተደምጠዋል። በዋሽንግተን ዲሲ፣በጀርመን ፍራንክፈርት፣በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያና በሌሎች ከተሞች በተካሄደው በዚህ ...

Read More »

በደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 2/2010) በደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተሰማ። በግቢው ውስጥ የእሳት ቃጠሎ መነሳቱም ተሰምቷል።–የቅስቀሳ ወረቀት በመበተን ላይ መሆኑም ታውቋል። በአዲግራት ዩኒቨርስቲ ሁለት ተማሪዎች መገደላቸውን ተከትሎ በአማራ ክልል በሚገኙ የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ግጭት ተቀስቅሷል። በወልዲያ ዩኒቨርስቲ በተነሳ ግጭት በትንሹ 4ተማሪዎች ተገድለዋል። በጎንደር ዩኒቨርስቲ የህወሃት መንግስት ከስልጣን እንዲወርድ በመጠየቅ እየተካሄደ ያለው ተቃውሞ መቀጠሉን ለማወቅ ተችሏል። በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የአማራና የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ ...

Read More »

በጨለንቆ በትንሹ ስድስት ሰዎች ተገደሉ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 2/2010) በሀረርጌ ጨለንቆ ዛሬ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ በትንሹ ስድስት ሰዎች መገደላቸው ታወቀ። በኢትዮጵያ ሶማሌ እና ኦሮምያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢም በተነሳ ግጭት ከ7 ያላነሱ ሰዎች ሲገደሉ፣ ከ14 ያላነሱ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የኢሳት ምንጮች ከስፍራው መረጃ አድርሰውናል። ለተቃውሞ መነሻ የሆነው ደግሞ ላለፉት ተከታታይ ወራት ከፍተኛ የሆነ ጥቃት ሲፈጽም የቆየው የሶማሌ ልዩ ሃይል በአንድ የኦሮሞ ተወላጅ ላይ ግድያ በመፈጸሙ ነው። የልዩ ሃይሉ ...

Read More »

ሳውዲ ሲኒማ ቤቶች እንዲከፈቱ ፈቀደች

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 2/2010) ሳውዲ አረቢያ ከ35 አመታት እገዳ በኋላ ሲኒማ ቤቶች በሀገሪቱ እንዲከፈቱ ፈቀደች። የሀገሪቱ ባህልና ማስታወቂያ ሚኒስቴር ሲኒማ ለመክፈት የሚያስችል ፍቃድ ዛሬ መስጠት ጀምሯል። ባለፈው ሰኔ አልጋ ወራሽነቱን የተቆናጠጡት መሐመድ ቢን ሳልማን በሳውዲ የተለያዩ ለውጦችን ለማድረግ በመንቀሳቀስ ላይ ሲሆኑ አሁን ሲኒማ እንዲታይ መፈቀዱ የዚሁ የለውጥ እንቅስቃሴ አካል ተደርጎ ተወስዷል። ራዕይ 2030 በመባል የሚታወቀውና በግዛቲቱ የተለያዩ ለውጦችን ለማድረግ በመንግስት የተያዘው ...

Read More »

የዋጋ ግሽበቱ ወደ 18 ነጥብ 1 በመቶ አሻቀበ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 2/2010) የምግብ ነክ ሸቀጦች የዋጋ ግሽበት ወደ 18 ነጥብ 1 በመቶ ማሻቀቡን የማዕከላዊ ስታቲትክስ ኤጀንሲ አስታወቀ። የተጠናቀቀው ህዳር ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 13 ነጥብ 6 በመቶ እንደነበርም የኤጀንሲው መረጃ አመልክቷል። በኢትዮጵያ ያለው የኑሮ ውድነት በቃላት መግለጽ የማይቻልበት ደረጃ ላይ መድረሱን መረጃዎች አመልክተዋል። የማዕከላዊ ስታቲትክስ ኤጀንሲ ባወጣው መረጃ ደግሞ አሁን ላይ የተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ባለፈው ከነበረው እንኳን በ2 መቶ ...

Read More »

ሕወሃት በስብሰባ ተጠምዷል ተባለ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 2/2010) የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በስብሰባ መወጠሩ ተሰማ። ሕወሃት በአቶ አባይ ወልዱና ወይዘሮ አዜብ መስፍን ምትክ አቶ ጌታቸው ረዳንና ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂምን እንዲሳተፉ ማድረጉ ታውቋል። የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ የውጭ ሀገር ጉዟቸው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ተሰርዟል።                                   በማያቋርጥ ስብሰባ የተጠመደው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በሀገራዊ፣ወቅታዊና ድርጅታዊ ጉዳዮች ላይ ለመወሰን በጠቅላይ ...

Read More »

የገደንቢ ወርቅ ማምረቻ የሚያደርሰው ማህበራዊ ቀውስ መባባሱ ተገለጸ

  (ኢሳት ዜና–ታህሳስ 2/2010) ለገደንቢ ወርቅ ማምረቻ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ያመጣው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ተባብሰው መቀጠላቸውን ቢቢሲ ገለጸ። ኩባንያው ወርቁን ለማጽዳት የሚጠቀምበት “ሳናይድ”የተባለው ኬሚካል የልብ፣የአእምሮና የነርቭ ህመሞችን እንደሚያስከትል ሙያተኞቹ ገልጸዋል። ሜድሮክ ወርቅ ማዕድን ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለገደንቢ ወርቅ ማምረቻ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ያመጣው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ተባብሰው መቀጠላቸውን ቢቢሲ በዘገባው አመልክቷል። የሚዲያ ተቋሙ በአካባቢው በአካል በመገኘት የሻኪሶ ነዋሪዎች፣የጤና ባለሙያዎች፣የወረዳው ...

Read More »

በኢየሩሳሌም ጉዳይ በተነሳው ብጥብጥ አንድ ሰው ተገደለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 29/2010) የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢየሩሳሌም የእስራኤል መዲና ስለመሆኗ እውቅና መስጠታቸውን ተከትሎ በተነሳው ብጥብጥ አንድ ሰው ሲገደል 200 ያህል ቆሰሉ። በእስራኤል በተያዘችው ዌስት ባንክ እንዲሁም በእስራኤልና ጋዛ ድንበር ላይ ከፍተኛ ግጭት ተከስቷል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ባለፈው ረቡዕ ኢየሩሳሌም የእስራኤል መዲና ነች አሜሪካም ኤምባሲዋን ከቴላቪቭ ወደ ኢየሩሳሌም ታዞራለች ማለታቸው ግጭት እንደገና እንዲያገረሽ ምክንያት ሆኗል። በፍልስጤም በመሀሙድ አባስ የሚመራው የፋታህ ፓርቲ ...

Read More »

ሕሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ባለማግኘታቸው ችግር ላይ መውደቃቸው ተሰማ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 29/2010) በኢትዮጵያ በውጭ ምንዛሪ እጥረት ሕሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ባለማግኘታቸው ችግር ላይ እየወደቁ መሆኑን ቢቢሲ ዘገበ። መድሃኒት አስመጪዎች የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ባለመቻላቸው በተለይ የልብና የስኳር ህሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ለማግኘት ተቸግረዋል። ቢቢሲ በአዲስ አበባ ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ህሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ማግኘት ባለመቻላቸው ችግር ላይ እየወደቁ መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም የስኳርና የልብ ህሙማን እለት እለት መድሃኒት የሚፈልጉ ቢሆንም በየመድሃኒት ቤቶቹ ዞረው ማግኘት አልቻሉም። ...

Read More »