በረመዳን ጾም ሙስሊሙ ተቃውሞውን አጠናክሮ ቀጥሎአል

ሐምሌ ፲፪(አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት በረመዳን ጾም ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የጀመሩት ተቃውሞ ይበርዳል የሚል እምነት የነበረው ቢሆንም፣ ተቃውሞው ከሳምንት ሳምንት እያየለ በመምጣቱ፣ የፌደራል ፖሊስ አባላት በአንዳንድ አካባቢዎች የሀይል እርምጃ መውሰድ ጀምረዋል። ከሀሙስ ጀምሮ በፌደራል ፖሊስ አባላት ክትትል ስር የነበሩት የወልድያ ሙስሊሞች በዛሬው እለት በመስጊዳቸው ውስጥ ታግተው መዋላቸውና አንዳንዶች መደብደባቸውን ሌሎች ደግሞ መታሰራቸው ታውቋል። የፌደራል ፖሊስ አባላት ወደ ...

Read More »

አንድነት ፓርቲ ተቃውሞ የሚካሄድባቸውን ቦታዎች ይፋ አደረገ

ሐምሌ ፲፪(አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፓርቲው ባወጣው የህዝባዊ ንቅናቄ እቅድ መሰረት ባህርዳር፣ ጅንካ፣ አርባምንጭ፣ አዳማ፣ ባሌ፣ ወሊሶ፣ ፍቼ፣ ጋምቤላ፣ አሶሳ እና አዲስ አበባ ለህዝባዊ ሰልፎች ሲመረጡ፣ መቀሌ፣ ወላይታ ሶዶ፣ አዋሳ፣ ድሬዳዋ፣ አምቦ፣ ደብረማርቆስና አዲስ አበባ በድጋሜ ለህዝባዊ ስብሰባዎች ተመርጠዋል። ሀምሌ 21 እና 28 በአዲስ አበባ 2 ቦታዎች እንዲሁም ሀምሌ 28 በወላይታ ሶዶና በመቀሌ ህዝባዊ ስብሰባዎች ሲደረጉ፣ በተመሳሳይ ...

Read More »

በአማራ ክልል ከ2001- 2004 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ብቻ 67 በገንዘብ የማይተመኑ ቅርሶች ተዘረፉ ፡፡

ሐምሌ ፲፪(አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት አጠናቅሮ ለክልሉ ባለስልጣናት ባቀረበው ሪፖርት ላይ እንተመለከተው የክልሉ ቅርስ ጥበቃ ቢሮ ታሪካዊ ቦታዎችን በመንከባከብና የቅርስ ዘረፋ እንዳይካሄድ በመከላከል በኩል በቂ ጥረት አላደረገም። በክልሉ ከ3000 በላይ የቅርስ መገኛ ተቋማት ቢኖሩም  ሙዝየም በማሰራት ቅርሶቻቸውን በጥንቃቄ ለእይታ የቀረቡት 13 ብቻ መሆናቸውን የኦዲት ሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡ በተለያዩ ዞኖች የሚጠፉ ታሪካዊ ቅርሶች ከአመት ...

Read More »

ኢትዮጵያዊው ፓይለት የ78 ሰዎችን ህይወት አተረፈ

ሐምሌ ፲፪(አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ረቡእ 78 ሰዎችን አሳፍሮ ከአዲስ አበባ  ወደ አክሱም ይበር የነበረው ቦምባርዴር ኪው 400 አውሮፕላን ማረፊያ ቦታው ላይ ሊደርስ ደቂቃዎች ሲቀሩት የጭስ መቆጣጠሪያው በመጥፋቱ፣ ፓይለቱ አውሮፕላኑን በአስቸጋሪ ሁኔታ በማሳረፍ የሰዎችን ህይወት እና የአየር መንገዱንም መልካም ስም ታድገዋል። ሱዳን ትሪቢውን አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ባለስልጣንን ጠቅሶ እንደዘገበው የጭስ መቆጣጠሪያው አውሮፕላኑ ለማረፍ አንድ ደቂቃ ...

Read More »

በወልድያ 2 ወር ያልሞላትን አራስ ጨምሮ ከ10 ያላነሱ ሙስሊሞች ታሰሩ

ሐምሌ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዘወትር አርብ የሚደረገውን ስግደት ተከትሎ ተቃውሞ ሊያስነሱ ይችላሉ ተብለው የተጠረጠሩ ከ10 ያላነሱ የወለድያ ከተማ ነዋሪዎች ታስረው ፍርድ ቤት መቅረባቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ተናግረዋል። ከታሰሩት መካከል ኢብራሂም ገበየሁ፣ ከድር ሙሀመድ፣ ወ/ሮ ሀያት ይማም፣ ወ/ሮ ነሲሳ አህመድ፣ ወ/ሮ ሀያት አህመድ ይገኙበታል። ወ/ሮ ሀያት አህመድ ሁለት ወር ያልሞላት አራስ ስትሆን፣ ወደ እስር ቤት የተወሰደችውም አዲስ ከተወለደው ...

Read More »

አንድነት የተቃውሞ ፊርማ የማሰባሰብ ሂደቱ በደህንነቶችና በፖሊስ ጥምረት እየተደናቀፈ ነው አለ

ሐምሌ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፓርቲው  በህገ ወጥ የዘመቻ እስር የሚሊዮኖች ድምፅ አይታጠፍም” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባ ከተማ የጸረ ሽብር አዋጁ በህገ መንግስቱ እውቅና የተቸራቸውን መብቶችን የሚጨፈልቅና ከህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች ጋር የሚጋጭ በመሆኑ መሰረዝ ይገባዋል የሚሉ ዜጎች ወደ ዋናው የፓርቲው በጽ/ቤት በመምጣት የተቃውሞ ፊርማቸውን እንዲያኖሩ የሚጠይቅ ‹‹ከሚሊዮኖች ለምን አንዱ አይሆኑም›› የሚል በራሪ ወረቀት በሁሉም የአዲስ አበባ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ወታደሮች የሞርሲና ቦዲ ሴቶችን የደፍራሉ ሲል አንድ የምርምር ተቋም አስታወቀ

ሐምሌ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኦክላንድ ኢንስቲቲዩት ባወጣው መግለጫ በኦሞ ሸለቆ የሚገኙ የሙርሲና የቦዲ ነዋሪዎች አካባቢያቸው ለሸንኮራ ገዳ ምርት ይፈለጋል በሚል በሀይል ቀያቸውን እንዲለቁ ከመደረጉ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መፈጸሙን ገልጿል። ድርጊቱ በአሜሪካ እና በእንግሊዝ መንግስት እርዳታና  እውቅና እየተካሄደ መሆኑም ገልጿል፡፡ የእንግሊዝ መንግስት የልማት ተራድኦ የውጭ ግንኙነት ክፍል ቃል አቀባይ ፣ ” የእኛ ድጋፍ ለዘመናት ...

Read More »

ኤርትራ በሶማሊያ ሰላም እንዳይኖር እየሰራች ነው ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኤክስፐርቶች አስታወቁ

ሐምሌ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሪዩተርስ ሚስጢራዊ ሰነድ አገኘሁ በማለት ባወጣው ዘገባ ምንም እንኳ የኤርትራ መንግስት የሶማሊያ ታጣቂ የሆነውን አልሸባብን አልደግፍም ቢልም ፣ ቡድኑ ግን ኤርትራ ታጣቂውን ሀይል መደገፉዋን በመቀጠሉዋ የተጣለባት ማእቀብ እንዳይነሳ አቤት ብሎአል።  ኤርትራ አብዲ ኑር ሰኢድ በተባለ የሶማሊያ ተወላጅ በኩል እርዳታ እንደምታደርግ ማረጋገጡን ቡድኑ ጠቅሷል። በቀረበባት ክስ ላይ ኤርትራ አስተያየቱዋን አልሰጠችም። ሩሲያ እና ጣሊያን በመርማሪ ...

Read More »

ኔልሰን ማንዴላ 95 አምስተኛ ልደታቸውን አከበሩ

ሐምሌ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የደቡብ አፍሪካው የነጻነት አባትና የመጀመሪያው ጥቁሩ ፕሬዚዳንት ኔልሰን ማንዴላ 95 ኛ አመት የልደት በአላቸውን በሆስፒታል አልጋቸው ላይ ሆነው አክብረዋል። ማንዴላን እንኳን አደረሰዎት ለማለት በሆስፒታሉ የተገኙት የወቅቱ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የማንዴላ ጤና መሻሻል እንዳስደሰታቸው ታናግረዋል። ” እንኳን አደረሰህ” ስላቸው በፈገግታ መልሰውልኛል ብለዋል ጃኮብ ዙማ። የአገሪቱ ነዋሪዎች የማንዴላን የ67 አመታት የፖለቲካ ህይወት ለመዘከር የ67 ደቂቃ ...

Read More »

በምስራቅ ኦሮምያ በልዩ ሀይሎች የተገደሉ ሰዎች በጅብ እንደተበሉ አንድ የሰብአዊ መብቶች ጠበቃ አስታወቀ

ሐምሌ ፲(አስር)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የምስራው አፍሪካ የሰብአዊ መብቶች ሊግ የተሰኘው ድርጅት ለኢሳት በላከው መረጃ ከ10 ቀናት በፊት ልዩ ሚሊሺያ እየተባሉ የሚጠሩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በ ኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ሀረርጌ ዞን በቀምቢ ወረዳ በጋራ ወሎ ቀበሌ በነዋሪዎች ላይ በፈጸሙት ጥቃት የ38 አመቱ ጎልማሳ ኢብራሂም ሄኖ፣ የ26 እና 27 አመት ወጣቶች ሙሀመድ ሙሳና ሙሀመድ የሱፍ ሲገደሉ፣ የ25 አመቱ ኑረዲን ...

Read More »