የአሜሪካ ፓሊስ ኢትዮጵያውያኑን በማደን ላይ ናቸው

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአሜሪካ ፖሊሶች ከኢትዮጵያ ለምስክርነት መጥቶ የጠፋን ኢትዮጵያዊ ዱካ ለማግኘት ፍለጋ ላይ መሆናቸውን ሲአትል ኒውስ ዛሬ ዘገበ፡፡ ካሳይ ወልደ ፃድቅ የተባለው ኢትዮጵያዊ አሜሪካዊያኖቹ ጥንዶች ከኢትዮጵያ በማደጎ ያመጧትን ልጅ ገድላችኋል ተብለው ለተከሰሱበት ወንጀል አቃቢ ህግ ለምስክርነት ማስረጃ ይሆን ዘንድ ብለው ነበር ከኢትዮጵያ ያመጡት፡፡ ካሳይ በፍርድ ሂደት ላይ ላለው ጉዳይ ባለፈው አርብ በማውንት ቬርኖን ካውንቲ ፍርድ ቤት ...

Read More »

250 ሺህ ዜጎች በግጭት በኦሮሚያና አማራ ክልሎች ተፈናቀሉ

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተባበሩት አለም አቀፍ የምግብ ድርጅት በኦሮሚያና አማራ ክልሎች በተለያዩ ግጭቶችና አደጋዎች ጉዳት ለደረሰባቸው 250 ሺህ ዜጎች አስቸኳይ እርዳታ መስጠት መጀመሩን ለኢሳት በላከው መግለጫ አስታወቀ፡፡ ድርጅቱ በኦሮሚያና አማራ ደርሶ ስለነበረው ግጭት ዝርዝር መረጃን ከመስጠት ቢቆጠብም 250ሺህ ለሆኑት ዜጎች ግን ጊዜያዊ የሆነ የምግብና የገንዘብ እርዳታ መስጠት ላይ እንደሆነ ገልጿል፡፡             ከአውሮፓ ህብረት ...

Read More »

በወልድያ የታሰሩት ፍርድ አጥተው በመሰቃየት ላይ ናቸው

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንዲት አራስን ጨምሮ ከ19 ያላነሱ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ለአንድ ወር ያክል በእስር ካሳለፉ በሁዋላ ዛሬ ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ምንም መፍትሄ ሳይሰጥ ወደ እስር ቤት እንደሚለሱ ተደርጓል። የአካባቢው ሰዎች ፍትህ ለማግኘት በፍርድ ቤቱ አካባቢ ቢሰባሰቡም በፖሊስ ሀይል እንዲበተኑ ተድርጓል። አንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት ፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ በቂ ማስረጃ ያልቀረበለት በመሆኑ ጉዳያቸውን መከታተል አቁሟል። ኢሳት ...

Read More »

አቶ መለስ ዜናዊን ለመዘከር በተለያዩ ከተሞች ማእከላት እየተገነቡ ነው

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ መለስ ዜናዊን አንደኛ የሙት አመት መታሰቢያ በማድረግ በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የዝክረ መለስ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው። በአዲስ አበባ 100 ሄክታር መሬት ስፋት ያለው ቦታ ከሀያት ሆስፒታል ፊት ለፊት ለመለስ ማእከል ግንባታ ተከልሏል። መስተዳድሩ ማእከሉን እንደሚያሰራ የአዲስ አበባ መስተዳድር አዲሱ ከንቲባ ድሪባ ኩማ የመሰረት ድንጋይ ባስቀመጡበት ወቅት ገልጸዋል። ግንባታው ምን ያክል ገንዘብ እንደሚፈጅ ግን ...

Read More »

ጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆ ከአምስት ዓመት እስራት በሁዋላ ተፈታች።

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የኦሮሚኛ ፕሮግራም ባልደረባ የነበረው ባለቤቷ ጋዜጠኛ ዳበሳ ዋቅጅራ ከሦስት ዓመት እስር በሁዋላ ከአገር መውጣቱን ተከትሎ   በኦነግ አባልነት ክስ ተመስርቶባት  ታስራ የቆየችው  ጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆ ከ እስር ተፈታች። በ 1995 ዓመተ ምህረት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እየሠራ ሳለ  ድንገት ለእስር የተዳረገው ጋዜጠኛ ዻበሳ ዋቅጅራ አንዳችም ክስ ሳይመሰረትበት ለሦስት ዓመታት በእስር ከቆየ በሁዋላ መፈታቱ ይታወሳል። ከእስር ቢለቀቅም ...

Read More »

የሙስሊም ጥያቄ እና የኢህአዴግ ስጋት

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የሕዝበ ሙስሊሙን ከ18 ወራት በላይ የዘለቀ እንቅስቃሴ በኃይል ለማፈን ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ እየወሰደ ያለው እርምጃ በሙስሊም አባላቱ ዘንድ ቅሬታ ማሳደሩ የግንባሩን ከፍተኛ አመራር ስጋት ውስጥ እንደጣለ የውስጥ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ አብዛኛዎቹ የግንባሩ ሙስሊም ከፍተኛ የአመራር አባላትን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ መካከለኛ፣ ዝቅተኛ አመራር አባላት መንግስት በሙስሊሙ ጥያቄ አፈታት ጉዳይ እየተከተለ ባለው ኃይል የተቀላቀለበት ...

Read More »

በቁጫ ወረዳ በርካታ ሰዎች ታሰሩ

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቁጫ ወረዳ ከማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በአካባቢው የተሰማራው የፌደራል ፖሊስ ከ50 በላይ ሰዎችን ማሰሩን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ከታሰሩት መካከል 6ቱ ሴቶች ናቸው። ባለፈው ሐሙስ የኢህአዴግ ካድሬዎችና ፖሊሶች መደብደባቸውን የሚያመለክት ሪፖርት መቅረቡን ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ አባላት ወደ አካባቢው በብዛት በማቅናት ሰዎችን በማሰር ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ መረጃዎችን በማቀባባል የአካባቢውን ህዝብ ለአመጽ ሊቀሰቅሱ ይችላሉ የተባሉ 106 ባጃጆችና ...

Read More »

በአማራ ክልል የመልካም አስተዳደር ችግር ስር የሰደደ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ተናገሩ

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመልካም አስተዳደር ኮማንድ ፖስት እየተባለ የሚጠራው መስሪያ ቤት በክልሉ ባሉ የአስተዳደር ቢሮዎች ባካሄደው ቅኝት የመልካም  አስተደዳር ችግር በክልሉ ተባብሶ መቀጠሉን ገልጿል፡፡ በተለይም በፍትህ ፤ በፖሊስ ፤ በማረሚያ ቤቶች ፤ በመሬት ፤ኢንቨስትመንት፤ መብራት እና ውሃ ደግሞ የችግሩ መለያ ቦታዎች መሆናቸውን ለክልሉ ካቢኔ የቀረበው ሪፖርት የቅሬታ ምንጭ መሆናቸውን ያወሳል፡፡ በክልሉም ከጊዜ ወደ ጊዜ የቅሬታዎች ቁጥር እየጨመረ ...

Read More »

ኦህዴድ ኢሳትን ለማስቆም እንደሚሰራ አስታወቀ

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በነቀምት ባደረጉት ስብሰባ ህዝቡ ኢሳትን እንዳይመለከት ካድሬዎች ከፍተኛ ስራ መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል። አመራሮቹ ኢሳት የአሸባሪ ድርጅቶች ንብረት በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ኢሳትን መመልከቱን እንዲያቆም ባለስልጣኖቹ ወትውተዋል። በስብሰባው ወቅት ለካድሬዎች ከተነገራቸው ነገር መካከል አንዱ ኢሳትን በሚመለከት ህግ ሊወጣ ነው መባሉ ነው። ምን አይነት ህግ እንደሚወጣ ግን ባለስልጣኖቹ ከማብራራት ተቆጥበዋል። ኢሳት በናይልሳት የሚያሰራጨው ስርጭቱ ...

Read More »

አልከሄር የኢትዮጵያን ጦር ክፉኛ ወቀሱ

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሱዳን አብየ ግዛት የሚገኘው የጥምር ኮሚቴ ስብሳቢዎች አንዱ የሆኑት አልከሄር አል ፋቲም አማጺ የሆነውን የሱዳን አብዮታዊ ግንባር በአካባቢው መኖሩ እያወቀ በስፍራው የሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር በዝምታ በማለፉ ክፉኛ ወቅስዋል:: አልከሄር አል ፋቲም ሰሜን ሱዳንን ወክለው የሚገኙ ሲሆን እንደሳቸው ገለጻ አማጺው ሃይል በምስራቅ አብየ ሰፍሮ እንደሚገኝ ገልጸዉ የኢትዮጵያን ጦር ዝምታ ግን የሰላሙን ሂደት እንዳያበላሸው አሳስበዋል:: ቅርብ ...

Read More »