በአዲስ አበባ ዛሬም ግጭት ተቀስቅሶ ዋለ

በአዲስ አበባ ዛሬም ግጭት ተቀስቅሶ ዋለ ( ኢሳት ዜና መስከረም 04 ቀን 2011 ዓ/ም ) በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራውን ኦነግ ለመቀበል የሚደረገውን ዝግጅት ተከትሎ የተነሳው ውጥረት እያየለ በመሄዱ ዛሬ በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት ተፈጥሯል። በርካታ ቄሮዎች ወደ መሃል አዲስ አበባ በመግባት የተለያዩ መፈክሮችን ሲያሰሙ የዋሉ ሲሆን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ በቄሮዎችና በአዲስ አበባ ወጣቶች መካከል በነበረው ድንጋይ ውርወራና ፖሊስ ግጭቱን ...

Read More »

በአማሮ ወረዳ ከአመት በላይ የዘለቀው ግጭት እንደገና አገረሸ

በአማሮ ወረዳ ከአመት በላይ የዘለቀው ግጭት እንደገና አገረሸ ( ኢሳት ዜና መስከረም 04 ቀን 2011 ዓ/ም ) ከ 15 ወር በላይ ያስቆጠረዉና መፍትሄ ያጣዉ በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ በሚገኙ የኮሬ ብሔረሰብ እና ቡርጂ ወረዳ በሚገኙ ቡርጂ ብሔረሰብ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን በሚኖሩ ጉጂ ብሔረሰቦች መካከል የተነሳዉ ግጭት ሰሞኑንም ተባብሶ በመቀጠል በሰዉ ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል። ከአማሮ ወረዳ ...

Read More »

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሐመድ እና ግብረአበሮቻቸው ላይ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርምራ ጊዜ ተሰጠባቸው።

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሐመድ እና ግብረአበሮቻቸው ላይ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርምራ ጊዜ ተሰጠባቸው። ( ኢሳት ዜና መስከረም 04 ቀን 2011 ዓ/ም ) የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ችሎት የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ አብረዋቸው የተከሰሱትን ሌሎች ተጠርጣሪዎችን አቤቱታ እና መርማሪ ፖሊስ ያቀረበውን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ አድምጧል። ተከሳሾቹ ለችሎቱ እንዳሉት ”ቤተሰብ እይጠየቀን አይደለም። ምግብና ህክምናም በአግባቡ እያገኘን አይደለም። ...

Read More »

የአማራ ዲሞክራሲ ሃይሎች ንቅናቄ በባህርዳር አቀባባል ተደረገላቸው

የአማራ ዲሞክራሲ ሃይሎች ንቅናቄ በባህርዳር አቀባባል ተደረገላቸው ( ኢሳት ዜና መስከረም 04 ቀን 2011 ዓ/ም ) አዲሃን በቅርቡ ወደ አገር ቤት መግባቱን ተከትሎ ዛሬ በባህርዳር ስታዲየም ከህዝቡ ጋር ተገናኝቶ አላማውን አስታውቋል። ህዝቡም ንቅናቄው ለ8 አመታት ላደረገው ትግል ምስጋናውን አቅርቧል። የአዲሃን ታጋዮች በስታዲየሙ ተገኝተው ወታደራዊ ትዕይት አሳይተዋል። አዲሃን ከዚህ በሁዋላ ራሱን ወደ ፓርቲ በመቀየር በሰላማዊ መንገድ ትግሉን እንደሚቀጥል አስታውቋል።

Read More »

የኮፊ አናን የቀብር ስነስርአት ተፈጸመ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 3/2011) የቀድሞው የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሃፊ የኮፊ አናን የቀብር ስነስርአት ዛሬ ተፈጸመ። የመጀመሪያውና እስካሁንም ብቸኛ ሆነው የተገኙት የመጀመሪያው አፍሪካዊ የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ኮፊ አናን በጥቂት ቀናት ህመም ሕይወታቸው ያለፈው ከሶስት ሳምንት በፊት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ነሐሴ 18/2018 ነበር። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ1997 እስከ 2006 ለ10 አመታት ያህል 7ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሆነው አገልግለዋል። በአንድ ወቅት ...

Read More »

አክቲቪስት ታማኝ በየነ ተፈናቃዮችን ጎበኘ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 3/2011) አክቲቪስት ታማኝ በየነ በድሬደዋ ከተማ የሚገኙ የሶማሌ ክልል ተፈናቃዮችን ዛሬ ጎበኘ። የድሬደዋ ከተማ ከንቲባ አቶ ኢብራሒም ኡስማን በተገኙበት ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር ሕዝባዊ ስብሰባ አካሂዷል። በእግረኛ የሙዚቃ ቡድን አቀባበል የተደረገለት አክቲቪስት ታማኝ በየነ የኢትዮጵያዊነትና የፍቅር ተምሳሌት የሆነችውን ድሬደዋን ከነበረችበት ተጎሳቁላ በማግኘቱ ማዘኑን ገልጿል። አክቲቪስት ታማኝ በየነ ከ30 አመት በፊት የሚያውቃት ድሬደዋ፣የፍቅርና የአንድነት ተምሳሌት የሆነው ሕዝቧ 27 አመታት በሐገሪቱ ...

Read More »

የአዲስ አበባን ጎዳናዎችና አደባባዮች ቀለም መቀባት ስህተት ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 3/2011) ለኦሮሞ ነጻነት ግንባር መሪ በሚደረገው አቀባበል የአዲስ አበባን ጎዳናዎችና አደባባዮች ቀለም መቀባት ስህተት ነው ሲል የአቀባበል ኮሚቴው ገለጸ። የኦነግ መሪ የአቀባበል ኮሚቴ ባሰራጨው መግለጫ የተሰቀሉት የድርጅቱ አርማዎችም ቢሆኑ ከአቀባበሉ በኋላ እንደሚነሱ አስታውቋል። ቄሮዎች ግጭትን ከሚፈጥሩ እንቅስቃሴዎች እንዲታቀቡም የአቀባበል ኮሚቴው ጥሪ አድርጓል። በሌላ በኩል ለኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የሚደረገው የአቀባበል ስነ ስርዓት ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ...

Read More »

የሕዝብ መገልገያዎች ላይ የኦነግን አርማ ማቅለም አይቻልም ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 3/2011) የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበርን ለመቀበል የግንባሩን አርማ ማውለብለብም ሆነ አደባባይ መውጣት የሚቻል ቢሆንም የሕዝብ መገልገያዎች ላይ አርማውን ማቅለም ግን የማይቻል መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር አሳሰቡ። ፖሊስ ኮሚሽነሩ ይህን ያሉት አቶ ዳውድ ኢብሳን ለመቀበል ከሚደረገው ዝግጅት ጋር ተያይዞ በአዲስ አበባ ወጣቶችና በኦሮሚያ ክልል ወጣቶች መካከል የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ በሰጡት መግለጫ ነው። ፖሊስ ጣቢያን ጭምር በተቀጣጣይ ነገር ለማቃጠል ሙከራ ...

Read More »

በኢትዮጵያ የተገኘው ለውጥ ዋጋ ተከፍሎ የመጣ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 3/2011) በኢትዮጵያ የተገኘውን ለውጥ ዋጋ ከፍለን ያመጣነው እንጂ በርቀት በማሸነፍ የመጣ ለውጥ የለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ገለጹ። በውጭ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎች ወደ ሐገር ቤት ሲገቡ ሔደን የምንቀበላቸው ሁላችንም አሸናፊ ስለሆንን ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የአሸናፊነት ስነልቡና አቃፊ ነው፣መግፋት ግን ተሸናፊነት ነው ብለዋል ወቅታዊውን የሃገሪቱን ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ። ይህን በማድረጋችን እኛን እንደተሸናፊ የቆጠሩ ...

Read More »

ከአርማና ሰንደቃላማ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት ተቀሰቀሰ

ከአርማና ሰንደቃላማ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት ተቀሰቀሰ ( ኢሳት ዜና መስከረም 03 ቀን 2011 ዓ/ም ) የፊታችን ቅዳሜ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡትን በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራውን የኦነግ አመራሮችን ለመቀበል በሚካሄደው ዝግጅት ላይ የኦነግን አርማ ለመስቀል እና መንገዶችንና አጥሮችን በኦነግ አርማ ለመቀባት አደባባይ የወጡ ወጣቶች፣ ድርጊቱን ከሚቃወሙ የአዲስ አበባ ወጣቶች ጋር ተጋጭተዋል። የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊሶች ግጭቱ ...

Read More »