ዚምባቢዌ ኢትዮጵያውያንን ይዛ አሰረች

ሰኔ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-37 ኢትዮጵያውያን በህወገጥ መልኩ የዝንባብዌን ድንበር በማቋረጣቸው መያዛቸውን ዴይሊ ኔሽን ዘግቧል። ኢትዮጵያውያኑ ባዞዎች በተሞላው የሊምፖፖ ወንዝ አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሙከራ ሲያደርጉ መያዛቸውን አገሪቱ ፖሊስ አስታውቋል። ጉዳያቸው እየታየ መሆኑን የገለጸው ፖሊስ፣ ምርመራው ሲጠናቀቅ ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስዳቸውም ገልጿል። በርካታ ኢትዮጵያውያን በእየአመቱ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሚጎርፉ ይታወቃል። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ስራ አጥነት፣ የኑሮ ...

Read More »

ኢቲቪ እንደእነ ቢቢሲ በኮርፖሬሽን ደረጃ ሊዋቀር ነው

ሰኔ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ከእነቢቢሲ ያጠናውን  ልምድ መሰረት አድርጎ ስያሜው ወደ ኢትዮጽያ ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬሽን እንዲቀየርለት የሚጠይቅ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማው ቀረበ፡፡ ድርጅቱ ለ19 አመታት ሲጠቀምበ ትየቆየውን አዋጅ ማሻሻል ያስፈለገው አደረጃጀቱን በማስተካከል የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጣ እንዲያስችለው ነው ተብሎአል፡፡ ለትርፍያልተቋቋመናተጠሪነቱለፓርላማውየሆነየመንግሥትየልማትድርጅትበመሆንበኮርፖሬሽንደረጃየሚዋቀረውኢትዮጵያብሮድካስቲንግኮርፖሬሽንየዚህኣይነትአደረጃጀትበልምድነትየቀሰምኩትከቢቢሲ፣ከኤስ፣ኤ፣ቢ.ሲ፣ከኬንያውኬ.ቢ.ሲእናከህንዱከኦልኢንዲያንስነውብሏል፡፡ አዋጁለዝርዝርዕይታለኮምቴተመርቷል።

Read More »

ለኢራቅ ችግር የፖለቲካ መፍትሄ እንደሚያሻው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናገሩ

ሰኔ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢራቅን እየጎበኙ የሚገኙት ጆን ኬሪ ይህን የተናገሩት አይ ኤስ ኤስ እየተባለ የሚጠራው በአብዛኛው በሱኒዎች የተሞላው ተዋጊ ሃይል የሰሜን ኢራቅን አካባቢዎች እየተቆጣጠረ መምጣቱን ተከትሎ ነው። ድርጅቱ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት አለው በሚል አሜሪካ እንደ አሸባሪ በመመልከቷ እውቅና አልሰጠችውም። ጆን ኬሪ ኢራቃውያን የችግሩን አሳሳቢነት ተረድተው እየወሰዱት ያለው እርምጃ ሊደነቅ ይገባል አሉ ሲሆን፣ የኢራቅ ፖለቲከኞች በአስቸኳይ ፖለቲካዊ ...

Read More »

የሶማሊው ክልል መሪ የመንግስት ደህንነቶች ሊገድሉዋቸው እንደሚችሉ በመጠቆም ጠባቂዎቻቸውን ቀየሩ

ሰኔ ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሶማሊ ክልል መሪ አብዲ ሞሃመድ ኡመር የፌደራሉ መንግስት የደህንነት ሰዎች ሊገድሉኝ ይፈልጋሉ በማለት ቀድሞ ሲጠብቁዋቸው የነበሩ ጠባቂዎቻቸውን በመቀየር አካባቢው በታማኞቻቸው በአይነ ቁራኛ እንዲጠበቅ እያደረጉ ነው። ካለፉት ሳምንታት ጀምሮ ወደ የፕሬዚዳንቱ ቢሮ ወደሚገኝበት አካባቢ የሚዘዋወሩ ሰዎች ልዩ ፍተሻ እየተደረገባቸው ነው። አቶ አብዲ ባለፈው ሳምንት ከ9 ዞኖችና ከ68 ወረዳዎች የተውጣጡ 1 ሺ 500 የሚሆኑ ከመላው ...

Read More »

የአንድነት የአዋሳ ሰልፍ “በእስር ተጀምሮ በእስር ተጠናቀቀ”

ሰኔ ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል አንድነት ፓርቲ በአዋሳ ሊያካሂደው የነበረው ሰልፍ ፣ የሰልፉ አስተባባሪዎችና የፓርቲው የአመራር አባላት በመታሰራቸው ምክንያት ሳይካሄድ ቀረ። ሰልፉ ከመካሄዱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በፓርቲው ቅስቀሳ የተደናገጡት የሚመስሉት የአዋሳ ባለስልጣኖችና ፖሊስ አባላት 37 የሚሆኑ በቅስቀሳ ላይ የተሰማሩ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ይዘው በተለያዩ እስር ቤቶች አስረዋቸዋል። በማግስቱ እስረኞችን ለመጠየቅና ስንቅ ለማቀበል ከሄዱት ...

Read More »

የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኛውን የዘነጋው የኢትዮጽያ መንግሥት የሲቪል ሰርቪስ ቀንን እያከበረነው

ሰኔ ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሠራተኛው በከፍተኛ የኑሮ ውድነት በደመወዝ መኖር የማይችልበት ስቃይ ውስጥ በሚገኝበትና ሲቪል ሰርቪሱ በገዥው ፓርቲ ቁጥጥር ሥር ሙሉ በሙሉ በወደቀበት በዚህ ወቅት ፣ ኢህአዴግመራሹ  መንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣናቱ በተገኙበት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ የሲቪል ሰርቪስ ቀንን በድምቀት እያከበረውይገኛል፡፡ በየዓመቱሰኔ 16 ቀንየሚከበረውየሲቪልሰርቪስቀንዘንድሮለስምንተኛጊዜየሚከበረው “በተደራጀሲቪልሰርቪስለውጥሠራዊትፈጣንናቀጣይነትያለውልማትበተግባርእናረጋግጥ” በሚልመርህመሆኑታውቋል፡፡ የሲቪልሰርቪስዘርፉከፖለቲካጋርተቀይጦሠራተኛውየኢህአዴግአባልበመሆንናባለመሆንመካከልባለበትእንዲሁምበየተቋማቱሠራተኛውአንድለአምስትእንዲደራጅበማስገደድበከፍተኛቁጥጥርውስጥባለበትሁኔታሲቪልሰርቪሱበለውጥሂደትላይነውበሚልጉሮወሸባዩመያዙእንዳሳዘናቸውያነጋገርናቸውአንዳንድየመንግሥትሠራተኞችተናግረዋል፡፡”ሙስናናየመልካምአስተዳደርችግሮችንለመቅረፍየሚያስችልየለውጥሠራዊትለመገንባትበሚልአንድለአምስትእንድትደራጅትገደዳለህ፣እምቢካልክትገለላለህ፡፡በየቀኑተሰብስበህትወያያለህ፣ይህንንምሪፖርትታደርጋለህ፡፡በዚህሁኔታአንዱከአንዱእየተፈራራናእየተጠባበቀ፣ሰዎችበችሎታናበሜሪትሳይሆንበፖለቲካአቋማቸውብቻተጠቃሚየሚሆኑበትስርዓትእንዲሰፍንሆኗል፡፡በዚህምምክንያትየመንግሥትሥራናአገልግሎትአሰጣጥእያሽቆለቆለ፣ምርታማነትእንዲቀንስበማድረግየሠራተኛውንየስራዋስትናጭምርአሳሳቢደረጃላይአድርሶታል” ሲሉያነጋገርናቸውገልጸዋል፡፡ በመንግሥትሁለተኛደረጃት/ቤትየሚያሰተምሩአንድመምህርበሰጡትአስተያየትከሲቪልሰርቪሱሠራተኞችየመምህራንቁጥርከፍተኛመሆኑንአስታውሰውበአሁኑሰዓትመምህራንእጅግበአነስተኛደመወዝየሰቆቃህይወትእየመሩመሆኑንአስታውሰዋል፡፡ “እኔበማስተምርበትትቤትዲግሪያላቸውመምህራንኑሮአቸውንለመደጎምሲሉበሰፈርአካባቢየድለላስራላይጭምርመሰማራታቸውን፣አንዳንዶቹምበተለይየደመወዝመዳረሻሰሞንበጣምስለሚቸገሩከሥራገበታቸውበተደጋጋሚስለሚቀሩበመማርማስተማሩሒደትላይአሉታዊተጽዕኖእየደረመሆኑ እውነትነው” ብለዋል፡፡ ሌላበአንድየሚኒስትርመ/ቤትበሕዝብግንኙነትሙያላይየተሰማራባለሙያእንዳስረዳውበመ/ቤቱውስጥሲካሄድየነበረውየቢፒአርእናየቢኤሲሲየለውጥፕሮግራሞችሠራተኛውሊቀበለውባለመቻሉከፍተኛወጪወጥቶበትተግባራዊሊሆንእንዳልቻለአስረድተዋል፡፡ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የዋጋ ንረት በማይፈጥር መልኩ ...

Read More »

ከምዕራብ ወለጋ የተፈናቀሉ እና አሁንም በአካባቢው ያሉ ዜጎች ፍትህ ማጣታቸውን ተናገሩ

ሰኔ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ከምእራብ ወለጋ ዞን ጊምቢና ከቄለም ወለጋ ዞን የተፈናቀሉ አማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ ያቀረበውን ዘገባ ተከትሎ ኢሳት ከጊምቢ በታች በሚገኘው አሹ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑትን እንዲሁም ተፈናቅለው ባህርዳር ከሚገኙት መካከል አንዳንዶቹን አነጋግሮ እንደተረዳው ፍትህ አጥተው የሚሰቃዩ ወገኖች በብዙ መቶዎች ይቆጠራል። አሹ ቀበሌ ውስጥ የሚኖረው በንግድ ስራ የሚተዳደረው ወጣት እንደተናገረው ወንድሙ አካባቢውን ለቆ ...

Read More »

አንድነት ፓርቲ በአዋሳ ለሚያደርገው የተቃውሞ ሰልፍ ችግር እንደገጠመው ታወቀ

ሰኔ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመጪው እሁድ በአዋሳ የሚካሄደውን የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ በቅስቀሳ ላይ የሚገኘው አንድነት፣ ሶሰትአባሎቹ እንደታሰሩበት አስታውቛል። አዲስ አበባ መስተዳድር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ያሬድ አማረ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ 3 ሰዎች መያዛቸውን ገልጸዋል። መስተዳድሩ የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ለመስጠት በሂደት ላይ በመሆኑ መቀስቀስ አትችሉም መባላቸውን የገለጹት አቶ ያሬድ፣ የእውቅና ጥያቄ ካስገቡ አንድ ወር ሞላቸው በመሆኑ በመስተዳድሩ የቀረበውን ...

Read More »

አዲሱ የጉምሩክ ረቂቅ አዋጅ ለገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር በፍርቤቶች ሊወሰን የሚገባ ጉዳዮችን እንዲወስን የተለ የመብት መስጠቱ አነጋጋሪሆነ፡፡

ሰኔ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ረቂቅ አዋጁ ሰሞኑን ለፓርላማው የቀረበ ሲሆን በዚሁ አዋጅ በዋና ዳይሬክተሩ ውሳኔ ብቻ ክስ የማይመሰረትባቸው ድንጋጌዎች ማካተቱ በፓርላማ አባላቱ ዘንድ ጥያቄ አስነስቷል፡፡ ረቂቅአዋጁ “ለሕዝብጥቅምሲባል በዋና ዳይሬክተሩ ውሳኔ ክስ የማይመሰረትባቸው አዲስ ሁኔታዎች በሚል ከዘረዘራቸው ውስጥ ወንጀል ፈጽሞአል የተባለ ሰው በዕድሜ መጃጀት ወይም በበሽታ ምክንያት ጉዳዩን በፍርድ ቤት መከታተል የማይችል ሲሆን ፣ጉዳዩ በክስሒደትውስጥቢያልፍብሔራዊደህንነትንወይምዓለምአቀፍግንኙነትንይጎዳልተብሎሲታመን፣የክሱመመስረትተመጣጣኝናሚዛናዊያልሆነየጎንዮሽጉዳትየሚያስከትልመሆኑከታመነበት፣ወንጀሉስልጣንላለውፍርድቤትሳይቀርብበመቆየቱአስፈላጊነትያጣከሆነ ክስ እንዳይመሰረትዋና ዳይሬክተሩ ...

Read More »

ሌ/ጄኔራል ዮሃንስ የጁባ የሰላም አስከባ ሃይል አዛዥ ሆኑ

ሰኔ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ሃይል በአብየ አዛዥ የሆኑት ሌ/ጄ/ዮሃንስ ገብረመስቀል በደቡብ ሱዳን የሚመሰረተውን የሽግግር መንግስት ሂደት እንዲመሩ ተሹመዋል። ከ100 ያላነሱ ወታደሮች ደቡብ ሱዳን የገቡ ሲሆን፣ አዛዡም ጁባ መግባታቸው ታውቓል። ጄ/ል ዮሃንስ በወር ከ20 ሺ የአሜሪካ ዶላር በላይ  እንደሚከፈላቸው የውስጥ ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። በአዲስ አበባ በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረት በደቡብ ሱዳን አዲስ የሽግግር ...

Read More »