የአሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ተጠናክሮ ቀጥሏል ተባለ

ኢሳት (የካቲት 25 ፥ 2008) በአዲስ አበባ የነበረው የአሽከርካሪዎችና የመኪና ባለቤቶች የስራ ማቆም አድማ በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ተጠናክሮ ቀጠለ። የኢሳት ምንጮት ከተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የላኩልን መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ በኦሮሚያ እና አማራ ክልል ከተሞች የስራ ማቆም አድማው አድማሱን እያሰፋ ቀጥሏል። በዛሬው እለት በኦሮሚያ ነቀምት ከተማ የተካሄደው አድማ ግጭቶችን ያስከተለ ሲሆን የመንግስት ሃይሎች በከፈቱት ተኩስ የከተማው ህዝብ ከፍተኛ ስጋት ላይ መውደቁን ለማረጋገጥ ...

Read More »

ኢትዮጵያንና ግብፅ ለመሸምገል እስራዔል ጣልቃ እንድትገባ ሃሳብ ያቀረቡት የግብፅ የፓርላማ አባል ከፓርላማ አባልነታቸው ተነሱ

ኢሳት (የካቲት 25 ፥ 2008) በቅርቡ የእስራዔል መንግስት ኢትዮጵያንና ግብፅ በአባይ ግድብ ዙሪያ ያላቸውን አለመግባባት ለመሸምገል ጣልቃ እንዲገባ ሃሳብን ያቀረቡ የግብፅ የፓርላማ አባል ከፓርላማ አባልነታቸው ተነሱ። የሃገሪቱ የፓርላማ አባላት የፓርላማ አባል የሆኑ ቶፊክ ኦካሻ ከእስራዔል አምባሳደር ጋር ያደረጉት የእራት ግብዣ ስነ-ስርዓት የሃገሪቱን የፓርላማ ስርዓት የጣሰ ተግባር ነው በሚል ከፍተኛ ተቃውሞ ማቅረባቸው ታውቋል። ይህንንም ተከትሎ ለግብፅ ፓርላማ የቀረበ ሃሳብ የፓርላማ አባሉ ...

Read More »

በጋምቤላ የእርሻ መሬት የወሰዱ ባለሃብቶች የተሰጣቸውን መሬት እንዲመልሱ ተወሰነ

ኢሳት (የካቲት 25 ፥ 2008) በጋምቤላ ክልል የእርሻ መሬቶችን የተረከቡ ወደ 100 አካባቢ ባለሃብቶች ክልሉ መሬቱን የሰጣችሁ በስህተት ነው በሚል መሬታቸውን እንዲመልሱ ተወሰነ። ባለሃብቶቹ በበኩላቸው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በማፍሰስ በህጋዊ መንገድ ወደስራ መግባታቸውንና የተሰጣቸው ማሳሰቢያ ቅሬታን እንዳሳሰረባቸው በመግለጽ ላይ መሆናቸውን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የፌዴራልና የክልሉ መንግስት ተናበው ባለመስራታቸው ችግሩ መፈጠሩን የሚናገሩት ባለሃብቶቹ፣ ከስድስት አመት በፊት መሬቱን በህጋዊ መንገድ ከክልሉ መንግስት ...

Read More »

በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች የሹፌሮች አድማ ቀጥሎአል

የካቲት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመረጃ ምንጮቻችን ከተለያዩ ከተሞች የላኩልን መረጃ እንደሚያሳያው በክልሉ ውስጥ ከሚገኙ ከተሞች መካከል የደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ሸዋ ሮቢት፣ አጣዬ፣ ቆቦ፣ ከምሴ፣ መርሳ ሾፌሮች አድማውን አጠናክረው በመቀጠላቸው፣የህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት በከፍተኛ ሁኔታ ተስተጓጉሏል። በኦሮምያ ደግሞ በነቀምቴ ተመሳሳይ አድማ በመካሄድ ላይ ነው። በወልድያ የተጀመረው አድማ ለሁለት ቀናት ከተካሄደ በሁዋላ ብዙዎች ታርጋቸው ተመልሶላቸው ስራ ጀምረዋል።የወረዳው ባለስልጣናት ...

Read More »

“በጸረ-ሽብርተኝነት ዘመቻው አጋራችን የሆነችውን ኢትዮጵያ ከከፋው የድርቅ አደጋ ልንታደጋት ይገባል!” ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለማቀፍ የልማት ኤጄንሲ አስተዳዳር ተናገሩ።

የካቲት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኤጄንሲው ኃላፊ ጋይለ ስሚዝ ይህን ያሉት ሀሙስ እለት የኢትዮጵያን ረሀብና መሰጠት ያለበትን የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ አስመልክተው ለአሜሪካ የአደጋ ጊዜ ደራሽ ቡድን በሰጡት መግለጫ ነው። እንደ ሲ ኤን ኤን ዘገባ በድርቅ ምክንያት የሚከሰተውን የደህንነት ስጋት ማስወገድ እንዲቻል የኦባማ አስተዳደር በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን የከፋ ድርቅ የሚቃኝ፣ የሚያስፈልገውን አስቸኳይ የእርዳታ መጠን የሚያሳውቅና ድጋፍ ...

Read More »

በኮንሶ የወረዳ አመራሮች ታሰሩ

የካቲት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኮንሶ ህዝብ ያቀረበው የአስተዳደር ጥያቄ ለበርካቶች መታሰር ምክንያት ከሆነ በሁዋላ፣ የክልሉ ርእሰ ብሄር ቦታው ድረስ በመሄድ ህዝቡን አነጋግረው መፍትሄ እንደሚሰጡ ቃል ከገቡ በሁዋላ፣ የወረዳው አመራሮች እርስ በርስ እየተጣሉና እየተካሰሱ ሲሆን፣የታሰሩ መኖራቸውም ታውቋል።አመራሮቹ “በህዝብ የተረገመና ያልተረገመ “በሚል በሁለት ተከፍለው አንደኛው በሌላኛው ላይ ክስ ከማሰማት አልፎ፣ የህዝብ ወገን ናቸው የተባሉ አመራሮች ታስረዋል። ...

Read More »

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በምስክርነት ለማቅረብ የተደረገው ጥረት ውድቅ ተደረገ

የካቲት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በአንደኛ ተከሳሽ አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ ላይ በቀረበው ክስ፣ ተከሳሹ ከግንቦት ሰባት ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር መጻጻፉን አቃቢ ህግ በክሱ ውስጥ ማስፈሩን ተከትሎ፣ ተከሳሽ አቶ አንዳርጋቸው ለምስክርነት እንዲጠሩላቸው ሲወተውቱ ቆይተዋል።ይሁን እንጅ እስር ቤቱ አቶ አንዳርጋቸውን ማቅረብ ባለመቻሉ፣ተከሳሽ ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር በተያያዘ ...

Read More »

የኦህአዴድ ካድሬዎች ለግምገማ ተጠሩ

የካቲት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ መላው የኦሮምያ ክልል የበላይና ከፍተኛ አመራሮች እና ካድሬዎች ከነገ ጅምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት ለሚቆይ ግምገማ አዳማ በሚዘጋጀው ክልል አቀፍ የካድሬዎች ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ታዘዋል፡፡ በየደረጃው የሚገኙ የኦህደዴ አባላት ከሰዓት ጀምሮ አዲስ አበባን ለቀው ወጥተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የኦሮምያ አካባቢዎች በክልሉ የተነሳውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ በአጋዚ ወታደሮችና ...

Read More »

በወልዲያ የተቀሰቀሰው የህዝብ ማመላለሻ አገልግሎት የስራ ማቆም አድማ ወደሌሎች ከተሞች መስፋፋቱ ተገለጸ

ኢሳት (የካቲት 24 ፥ 2008) በወልዲያ ከተማ የተጀመረው የአሽከርካሪዎች የመኪና ባለቤቶች የስራ ማቆም አድማ ዛሬ ለሁለተኛ ቀን መቀጠሉ ታወቀ። ትናንት ከቀትር በኋላ የተጀመረው አድማ ዛሬ ሌሎች የሰሜን ወሎ ከተሞች መቀላቀላቸውን ያገኘነው መረጃ የመለክታል። በደሴ ዛሬ በስፋት የተጀመረ ሲሆን ኮምቦልቻ ውርጊዛ፣ ውጫሌ፣ ቆቦና አላማጣ ከተሞችም በተመሳሳይ የአሽከርካርዎች አድማ ተመቷል። በወልዲያ የመንግስት ባለስልጣናት ማስፈራሪያና ማታለያ የተንጸባረቀበት ስብሰባ ለተሽከርካሪ ባለሃብቶች አዘጋጅተው የነበረ ቢሆንም፣ ...

Read More »

ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ህጻናትና በእርግዝና ላይ የሚገኙ እናቶች ለከፋ የምግብ እጥረት መጋለጣቸው ተገለጸ

ኢሳት (የካቲት 24 ፥ 2008) በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለተጋለጡ ሰዎች መቅረብ ያለበት ድጋፍ በወቅቱ ባለመድረሱ ምክንያት ከሁለት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ህጻናትና በእርግዝና ላይ የሚገኙ እናቶች ለከፋ የምግብ እጥረት መጋለጣቸውን የእርዳታ ተቋማት ገለጡ። ተረጂዎችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት እስከቀጣዩ ወር ድረስ አፋጣኝ ምላሽ ማግኘት ካልተጀመረም በሃገሪቱ መጠነ-ሰፊ የሆነ የሰብዓዊ ቀውስ ሊከሰት እንደሚችል ተቋማቱ አሳስበዋል። በኢትዮጵያ የአለም ምግብ ፕሮግራም ተወካይ የሆኑት ጆን ...

Read More »