በሰሜን ጎንደር የሚገኘው የመኢአድ ጽህፈት ቤት አባሎቻቸው በገፍ መታሰራቸውን ገለጠ

ሰኔ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ጽህፈት ቤቱ ለኢሳት በላከው መረጃ እንዳመለከተው በኢትዮጵያ ውስጥ በዜጎች ላይ የሚደርሰው እስራት፣ ግርፋት፣ ስደትና ረሀብ ከልክ አልፎአል ብሎአል። በሰሜን ጎንደር በጭልጋ ወረዳ የመኢአድ ም/በት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ መለሰ አስሬ ግንቦት23 ከቀኑ በ10 ሰአት ከ10 በላይ በታጠቁ የፌደራል ፖሊሶች በሀይል ተወስደው የደረሱበት አለመታወቁን፣ የጃናሞራ ወረዳ መኢአድ ም/ቤት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ስለሺ ጥጋቤነህ ግንቦት 23 ...

Read More »

በተለያዩ አገራት የሚገኙ የኢምባሲ ሰራተኞች ለአባይ ግድብ በዶላር አናዋጣም በማለት ያቀረቡት ተቃውሞ ምላሽ አገኘ

ሰኔ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሰራተኞች በተለያዩ አገሮች ወደሚገኙ ኢምባሲዎች ሲላኩ በዶላርና በብር ይከፈላቸዋል። ይህን ተከትሎም የውጭ ጉዳይ መስሪያቤት ሰራተኞቹ ለአባይ ቦንድ ግዢ ቃል የገቡትን በዶላር እንዲከፍሉ መመሪያ ያወርዳል። የኢምባሲው ሰራተኞች በበኩላቸው ክፍያውን በብር እንጅ በዶላር እንደማይከፍሉ ተቃውሞዋቸውን ለውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባለስልጣናት አቤት በማለት ተቃውሞአቸውን ገልጠዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የኢምባሲ ሰራተኞች ተቃውሞ ስጋት ላይ ስለጣለው፣ ...

Read More »

ሚድሮክ፤ የመንገድ ፕሮጀክቶቹን እንዲነጠቅ ተወሰነ

ሰኔ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ የመንገድ ጨረታ ዳግም እንዳይሳተፍ ተባለ። የሼህ መሀመድ ሁሴን  አል-አሙዲ ንብረት የሆነው ሚድሮክ ኮንስትራክሽን  በአዲስ አበባ  የሚገነባቸውን ሦስት የመንገድ ፕሮጀክቶች እንዲነጠቅ ውሳኔ መተላለፉን ሪፖርተር ዘገበ። ጋዜጣው  የ አዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣንን በመጥቀስ  እንደዘገበው፤ ሚድሮክ  የጀመራቸውን የመንገድ ፕሮጀክቶች  እንዲነጠቅ  የተወሰነው  በተገቢው ጊዜ  አጠናቅቆ ሊያስረክብ ባለመቻሉ ነው። ከዚህም ባሻገር ሚድሮክ በከተማው የመንገድ ግንባታ ጨረታ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ከቡና ጋር በተያያዘ በአለም ላይ ያላትን ስም ልታጣ ትችላለች ተባለ

ሰኔ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በያዝነው አመት ኢትዮጵያ ለውጭ ያቀረበችው ቡና በግማሽ ቀንሶአል።  ባለፉት ስምንት ወራት የተገኘው የቡና ኤክስፖርት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ 447 ሚሊዮን ዶላር  ቅናሽ አሳይቷል። በኢትዮጵያ ቡና ላይ ከአዘገጃጀት ጉድለት አንፃር የተከሰተን የጥራት ችግር እንዲሁም በላኪዎች የሚታየው ተደጋጋሚ ማጭበርበርን ተከትሎ ቡና ገዥ አገሮች ሙሉ በሙሉ ፊታቸውን ወደ ብራዚል ማዞራቸው እየተገለጠ ነው፣ ዋና ዋና ...

Read More »

የፌደራሉ መንግስትና የሲዳማ ዞን በአዋሳ እጣ ፈንታ ላይ ውጥረት የበዛበት ውይይት እያካሄዱ ነው

ሰኔ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የፌደራል መንግስቱ አዋሳን በስሩ ለማድረግ እቅድ እንዳለው ሲታወቅ፣ የሲዳማ ዞን በበኩሉ ድርጊቱን ይቃመዋል። በቅርቡ በተደረገው ውይይት ላይ አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበር፣ የሲዳማ ዞን ባለስልጣናትም የፌደራል መንግስቱ ባለስልጣናት የሚመሩትን ስብሰባ ረግጠው መውጣታቸውንና ጉዳዩን ከፌደራል መንግስት ባለስልጣናት እውቅና ውጭ እያካሄዱት ነው። አዲሱ ውዝግብ የአዋሳን ህዝብ ትኩረት መያዙም ታውቋል። በ1994 ኣም በፌደራል መንግስትና በዞኑ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት  ...

Read More »

ለአባይ ግድብ ማሰሪያ ያለፈቃዳቸው ደሞዛቸው የተቆረጠባቸው እና ተቃውሞ ያሰሙ ኢትዮጵያውያን አስፈላጊው የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተባለ

ሰኔ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የደቡብ ተወላጆች  ለኢሳት እንደገለጡት ያለፈቀዳቸውን ለህዳሴ ግድብ ማሰሪያ  በሚል የተቆረጠው ገንዘብ እንዲመለስላቸው በመጠየቃቸው ነው አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድባቸው የሚል ደብዳቤ የደረሳቸው። ” የህዳሴን ግድብ ገንዘብ አሰባሰብን ይመለከታል”   በሚል ርእስ በተጻፈው ደብዳቤ ላይ ለግድቡ አናዋጣም ባሉት ላይ አስፈላጊው የማስተካከያ እርምጃ የሚወሰደው ጸረ ልማት ሀይሎች ተብለው በመፈረጃቸው  ነው። “መንግስት” ይላል የደብዳቤው መግቢያ ” ...

Read More »

የኢትዮጵያ መንግስት የኢንተርኔት አፈናውን መቀጠሉን ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ አስታወቀ

ሰኔ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ድርጅቱ እንደገለጠው የኢትዮጵያ መንግስት የኢንትርኔት ተጠቃሚዎች ስማቸውን ሳይገልጡ የሚጠቀሙበትን እና እንዳይታዩ የታገዱ ድረገጾችን ለማየት የሚጠቅመውን ቶር ኔት ወርክ ዘግቷል። ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ  ማተሚያ ቤቶች አዲስ ያወጡትን ቅድመ ምርምራን የሚያጠናክረውን ውልም ተችቶአል። ፓርላማው በቅርቡ አዲስ የወጣውን የቴሌኮሚኒኬሽን ህግ ማጽደቁ ይታወሳል። በአዲሱ ህግ ከየቴሌኮሚኒኬሸን መሳሪያዎች ጋር የተያያዙ ወንጀሎች  ከ10-15 ዓመታት በሚደርስ ጽኑ እሥራትና ከ100ሺ ...

Read More »

አልሸባብ ፕሬዚዳንት ኦባማንና ውጭ ጉዳይ ሚኒሰትሩዋን ለመግደል የሚያስችል መረጃ ለሚሰጡ ሁሉ እንደሚከፍል አስታወቀ

ሰኔ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-አልሸባብ ፕሬዚዳንት ኦባማንና ውጭ ጉዳይ ሚኒሰትሩዋን ለመግደል የሚያስችል መረጃ ለሚሰጡ ሁሉ ገንዘብ እንደሚከፍል አስታወቀ የሶማሊያ ታጣቂ ሀይል ይህን መልስ የሰጠው የባራክ ኦባማ አስተዳዳር የአልሸባብ መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚሰጥ ማስታወቁን ተከትሎ ነው። የአልሸባብ የቆዩ መሪ የሆኑት ሼክ ሾንጎሌ እንደተናገሩት ፕሬዚዳንት ኦባን ለመግደል የሚያስችል በቂ መረጃ ለሚያመጣ ሰው 10 ግመሎችን ይሸልማሉ፤ በአንጻሩ ሂላር ...

Read More »

በዋልድባ ገዳም አካባቢ ማይጋባ በሚባል ቦታ ላይ በፌደራል ፖሊስና እና በአርሶ አደሩ መካከል በተነሳ ግጭት 15 ሰዎች ተገደሉ

ሰኔ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት ግጭቱ የተነሳው ግንቦት25 ሲሆን፣ የፖሊስ አባላቱ የአካባቢው አርሶአደሮች ቤቶቻቸውን እንዲያፈርሱ ሲጠይቁ አርሶአደሮች ለማፍረስ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ በተነሳ ግጭት ነው ፖሊሶችና አርሶአደሮች የተገደሉት። በተመሳሳይ ዜና ደግሞ በዋልድባ አካባቢ በምትገኘዋ የዛሬማ ከተማ የሚገኙ ወጣቶች በትናንትናው እለት በርካታ መኪኖችን አግተው ውለዋል። የፌደራል ፖሊስ አባላት ከወታቶች ጋር በፈጠሩት ግጭት በርካታ ወጣቶች ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከ60 ...

Read More »

ሰኔ 1 ዛሬ በተለያዩ አካባቢዎች እየታሰበ ነው

ሰኔ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በምርጫ 97 የመለስ መንግስት የህዝብ ድምጽ ማጭበርበሩን ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ በግፍ የተገደሉ ኢትዮጵያውያንን በአዲስ አበባ እና በመላው አለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እየዘከሩት ነው። ከመኢአድ የተለዩት እና በዶ/ር ታዲዮስ የሚመራው መኢአድ አባላት በዛሬው እለት በመቶዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸውን በመያዝ እለቱን አስበው ውለዋል። 22 አካባቢ ከሚገኘው የአቶ ተስፋ ድረቤ ቤት በርካታ ወጣቶች በተገኙበት ቀኑን በግጥም እና በተለያ  ...

Read More »