.የኢሳት አማርኛ ዜና

በሩሲያ አንድ ጅራታም ኮከብ ወደቀ

የካቲት ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ቢቢሲ እንደዘገበው ጅራታም ኮከብ ወይም ሜትዮሩ የወደቀው በሩሲያ የኡራል ተራራ ላይ ሲሆን፣ 950 የሚሆኑ ሰዎች ተጎድተዋል። አብዛኞቹ በተለያዩ መጠኖች ቁስለት የደረሰባቸው ሲሆን፣ 46 ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል። ፕሬዚዳንት ፑቲን ሜትዮሩ በመኖሪያ ሰፈር ላይ ባለመውደቁ እግዚአብሄርን አመስገንዋል። ሜትዮሩ ከመሬት ጋር በሚላተምበት ጊዜ ከፍተኛ የሆነ ፍንዳታ መሰማቱ ታውቋል። አንዳንድ ፖለቲከኞች በበኩላቸው የወደቀው ሜትዮር ሳይሆን የአሜሪካ አዲስ የጦር ...

Read More »

በጎንደር መድሀኒዓለም ቤ/ክ የተጠለሉ 48 ባህታዊያንን ወደ መጡበት ዋልድባ መወሰዳቸው ታወቀ

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ባህታዊያኑ ከጥር 2 ቀን 2005 ዓም ጀምሮ በጎንደር ከተማ በሚገኝ መድሀኒአለም ቤ/ክርስቲያን ውስጥ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገላቸው ተጠልለው ቆይተዋል። ትናንት ባህታዊያኑ ከቀኑ ስምንት ሰአት ላይ በአውቶቡስ ተጭነው ወደ አልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን የዘገብን ሲሆን፣ ወኪላችን ሂደቱን ተከታትሎ እንደዘገበው ባህታዊያኑ የተወሰዱት ፣ ከተለያዩ የአማራ ክልል የተውጣጡ የሀይማኖት አባቶች ችግሩን በሽምግልና እንፈታዋለን የሚል ሀሳብ ካቀረቡ በሁዋላ ነው። ...

Read More »

33ት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጂሀዳዊ ሀረካትን ተብሎ በኢቲቪ የቀረበውን ፊልም አወገዙ

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በመጪው  የአዲስ አበባ እና የአካባቢ ምርጫ ላለመሳተፍ የወሰኑ 33ቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ” መንግስት ጅሀዳዊ ሃረካት በሚል ርእስ በኢቲቪ ያስተላለፈው ፊልም ዋና አላማ የህዝብን የዘመናት አብሮነት በመሸርሸርና የመብት ጥያቄ የሚያነሳን ከሽብረተኝነትና ጦርነት ጋር በማያያዝ ህዝብን ለማሸማቀቅ ሆኖ በውጤቱም ህዝብ በአገሩ ላይ ያለውን የባለቤትነትና ሃላፊነት ስሜት በመናድ አንገት ማስደፋትና መብት ጠያቂዎችን በመነጣጠልና መከፋፈል ጥያቄዎችን ማደፈንና ...

Read More »

የፕሬስ ነጻነት አስከፊ ከሆነባቸው 10 አገራት ኢትዮጵያ አንዷ ናት ተባለች

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ሲፒጄ  የፕሬስ ነጻነት አደጋ ውስጥ የወደቀባቸው 10 የአለም አገራት በማለት በግንባር ቀደምነት ያስቀመጣቸው አገሮች ብራዚል፣ ኢኳዶር፣ ኢትዮጵያ፣ ኢራን፣ ፓኪስታን፣ ራሺያ፣ ሶማሊያ ፣ ሶሪያ፣ ቱርክ እና  ቬትናም ናቸው። ኢትዮጵያ የጸረ ሽብር ህግ በማውጣት ጋዜጠኞች በእስር ቤት እንዲማቅቁ ማድረጓን በዚህ ድርጊቷም   ከኤርትራ በመቀጠል የሁለተኛነት ስፍራ መያዙዋ ተጠቅሷል። አምና 4 ጋዜጠኞች ፣ ከ2007 ጀምሮ ደግሞ በድምሩ ...

Read More »

በኢትዮጵያ ነጋዴዎች ተቃውሞአቸውን እየገለጡ ነው

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንዳለው ምርታቸውን ወደ ውጭ አገራት የሚልኩና የሚያስገቡ ነጋዴዎች ፣ መንግስት የጣለባቸውን የአባይ ግድብ ቦንድ ግዢም ሆነ ሌሎች የመንግስት እዳዎችን ለመክፈል የተቸገሩት ከውጭ ምንዛሬ እጥረት ጋር ተያይዞ ስራቸው በመዳከሙ ነው። የተለያዩ የንግድ ድርጅቶች ኤልሲ ከፍተው እቃዎችን ለማስገባት በማይችሉበት ደረጃ ላይ በመድረሳቸው ድርጅታቸውን በመዝጋት ሰራተኞቻቸውን ለማሰናበት ጫፍ ላይ መድረሳቸውን ነጋዴዎች እንደሚገልጹ ...

Read More »

የሶማሊ ልዩ ሚሊሺያዎች በነዋሪዎች ላይ የፈጸሙትን አሰቃቂ ግድያ ኢሳት ይፋ አደረገ

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በምእራባዊያን አቆጣጠር ማርች 16፣ 2012 በኢትዮጵያዋ የሶማሊ ክልል ፣ በጋሻሞ ወረዳ በክልሉ መንግስት የሚተዳዳሩት ልዩ ሚሊሺያዎች አንድ ወጣት ይገድላሉ። የወጣቱን መሞት ተከትሎ ከወረዳው ህዝብ የተውጣጡ ሰዎች ” አሁንስ በቃ ” በማለት ገዳዩን የሚሊሺያ አባል ተከታትለው  ይገድሉታል። የልዩ ሚሊሺያ ሀይሉ አባላት በተደጋጋሚ ወደ አካባቢው በመሄድ ነዋሪዎችን ሲገድሉ፣ ሴቶችን ሲደፍሩና ንብረት ሲዘርፉ መቆየታቸውን የአካባቢው  ሰዎች ...

Read More »

ከዋልድባ ተሰደው በጎንደር መድሀኒዓለም ቤ/ክ የተጠለሉ 48 ባህታዊያን ታፍሰው ተወሰዱ

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት የጎንደር ዘጋቢ በስፍራው ተገኝቶ እንደዘገበው  ባህታዊያኑ ከጥር 2 ቀን 2005 ዓም ጀምሮ  መድሀኒአለም ቤ/ክርስቲያን ውስጥ በሚገኝ አንድ አዳራሽ ውስጥ ከሰዎች ጋር እንዳይገናኙ ተደርጎ በጥብቅ ቁጥጥር  ሲጠበቁ  ቆይቷል። በዛሬው እለት ባህታዊያኑ ከቀኑ ስምንት ሰአት ላይ በአውቶቡስ ተጭነው ወደ አልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። የአካባቢው ወጣቶች ከባህታዊያኑ ጋር አብረን እንሄዳለን የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ አካባቢው በፖሊስ ...

Read More »

የኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ለሁለት ሊከፈል ነው

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ሁለት ቦታ ለመክፈል እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ በቂ ጥናት ያልተደረገበትና ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን ያገናዘበ ባለመሆኑ መንግሥት ዕርምጃውን  እንዲገታ እና ዳግም እንዲያጤን  በዓለማቀፍ አበዳሪዎች መጠየቁን ሪፖርተር ዘገባ። እንደ ጋዜጣው ዘገባ የዓለም ባንክ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክና ሌሎች ዓለም አቀፍ አበዳሪዎችም ኮርፖሬሽኑ የመዋቅር ለውጥ የሚደረግበት ከሆነ ብድር ላለመስጠት እያንገራገሩ ናቸው፡፡ መንግስት በአሁኑ ጊዜ ...

Read More »

በደቡብ ክልል በማጅራት ግትር በሽታ አሁንም ሰዎች እየሞቱ ነው

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት የደቡብ ዘጋቢ እንደገለጠው በሲዳማ ዞን በሰበዲኖ ወረዳ በበሽታው ሶስት ሰዎች የሞቱ ሲሆን፣ በአዋሳ ከተማ ደግሞ አንድ ታዳጊ ወጣት ሞቷል።  ከመንግስት የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በዞኑ ከ100 በላይ ሰዎች በበሽታው በመያዛቸው ህክምና እየተደረገላቸው ነው። በአዋሳ በሁሉም ጤና ማእከላት ክትባት ለመስጠት እየተሞከረ ሲሆን፣ በጭኮ፣ አለታ ወንዶ፣ ይርጋለም፣ በደራ እና  በቤኔሳ ክትባቱ ባለመጀመሩ ህዝቡ መደናገጡ ታውቋል።

Read More »

አንድነት ፓርቲ በአራት ወራት ውስጥ 1 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዷል

የካቲት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ፓርቲው ለመገናኛ ብዙሀን ባሰራጨው መረጃ፣ ገንዘቡን የሚያሰባስበው፣ በመንግስት ቁጥጥር ስር ያለው ብርሀንና ሰላም ማተሚያ ቤት በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ የመጣውን ፍኖተ-ነጻነት ጋዜጣን ለማተም ፈቃደኛ ባለመሆኑ የራሱን ማተሚያ ቤት ለማቋቋም ነው። ፓርቲው ብቸኛ ልሳኑ የሆነውን ፍኖተ-ነጻነትን በመንግስት የአፈና ፖሊሲ የተነሳ ለማሳተም እንዳልቻለ ገልጿል። ይህንን ችግርም ለመቅረፍ ድርጅቱ በሚቀጥሉት አራት ወራት 1 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ...

Read More »