.የኢሳት አማርኛ ዜና

ቻርለስ ቴለር ወደ አፍሪካ ሄደው የእስር ጊዜያቸውን እንዲፈጽሙ ጠየቁ

ሰኔ ፲(አስር)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞው የላይቤሪያ መሪ ቻርለስ ቴለር በሴራሊዮን እኤአ ከ1991-2002 በነበረው የእርስ በርስ ጦርነት እጃቸው አለበት በሚል በሄግ ኔዘርላንድስ በተቋቋመው ልዩ ፍርድ ቤት  የ50 አመት እስር ተፈርዶባቸዋል። የእስር ጊዜያቸውን በእንግሊዝ የሚያሳልፉት ቴለር፣ 15 ልጆቻቸውን በየጊዜው ለማየት ባለመቻላቸው ወደ ሩዋንዳ ተወስደው እንዲታሰሩ ጥያቄ አቅርበዋል። ከቤተሰቦቻቸው እርቀው እንዲታሰሩ መደረጉ አለማቀፍ ህግን የሚጥስ መሆኑን የቴለር ጠበቆች ተናግረዋል። ይሁን እንጅ ...

Read More »

በኦሮምያ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ ከታሰሩት መካከል አንዳንዶች ሲፈቱ ሌሎች ደግሞ ፍርድ አጥተው እየተሰቃዩ ነው

ሰኔ ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ በኦሮምያ ተነስቶ የነበረውን ተቃውሞ ተንተርሶ ከተያዙት በሺ ከሚቆጠሩ ወጣቶች መካከል የተወሰኑት ከእስር ሲለቀቁ፣ አብዛኞቹ አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ። የክልሉ ወኪላችን እንደሚለው በወለጋ፣  በአንቦና አጎራባች ወረዳዎች የታሰሩ በርካታ ወጣቶች አሁንም ፍትህ አጥተው በእስር ላይ ሲሆኑ በቡራዩ ታስረው ከነበሩት መካከል 3ቱ ዛሬ በዋስ ተለቀዋል። ጋዲሳ ጉደታ፣ ቱፋ በክሩ እና ጉዲሳ ...

Read More »

የሞያሌ ነዋሪዎች የደህንነት ክትትሉ እንዳስመረራቸው ገለጹው

ሰኔ ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-2 የአልሸባብ አባላት ናቸው የተባሉ የሶማሊ ተወላጆች መያዛቸውን መንግስት ካስታወቀ በሁዋላ፣ በኢትዮጵያዋ የድንበር ከተማ ሞያሌ ከፍተኛ ጥበቃ እየተካሄ መሆኑንና በዚህም የተነሳ መንግስት በህዝቡ ላይ የሚያደርገው ክትትል እንዳስመረራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። መውጫ መግቢያ ማጣታቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ የደህንነት ሃይሎችና ታጣቂዎች ማታ ማታ በግለሰቦች ቤት ሳይቀር እየገቡ ፍተሻ ያካሂዳሉ ብለዋል። በምሽት ለመውጣት መቸገራቸውን የሚገልጹት ነዋሪዎች፣ የአካባቢውን ...

Read More »

የአዳዲሶቹ የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታ መጓተቱትን መረጃዎች አመለከቱ

ሰኔ ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዳዲስ የስኳር ፋብሪካዎች ፕሮጀክቶችና የነባር የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች የግንባታ ስራዎች አፈጻጸም እጅግ ደካማ መሆኑን ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ጠቁሟል። ለዚህደካማአፈጻጸምሚኒስቴሩበዋንኛነት ያስቀመጠውምክንያትከስራውስፋትናውስብስብነትአንጻርያጋጠመውትልቅየማስፈጸምአቅምማነስነውብሏል፡፡በቀጣይዓመትበሚጠናቀቀውየመንግስትየዕድገትናየትራንስፎርሜሽንዕቅድየመጀመሪያዎቹሶስትዓመታትማለትምከ2003-2005 ኣ.ምየአዳዲስስኳርልማትፕሮጀክቶችየሚካሄዱትከዚህበፊትምንምየመሰረተልማትባልተዘረጋባቸውናለግንባታስራየሰለጠነየሰውኃይልበማይገኝባቸውአካባቢዎችበመሆኑበዕቅድዘመኑውስጥየመጀመሪያዎቹሁለትዓመታትማለትም 2003 እና 2004 የመንገድናሌሎችየአዋጪነትየጥናትስራዎችመከናወናቸውንመረጃውይጠቅሳል፡፡ በመሆኑምበእነዚህኣመታትለቀጣይስራመደላድልከመፍጠርባለፈተጠናቅቆ ወደምርትየገባፕሮጀክትአልነበረም፡፡ የነባርስኳርፋብሪካዎችየማስፋፊያፕሮጀክቶችየግንባታስራዎችመካከልየወንጂናየፊንጫስኳርፋብሪካዎችተጠናቅቀውበ2005 ኣ.ምወደስራየገቡሲሆንየተንዳሆስኳርፋብሪካበዚህዓመትወደስራእንደሚገባመረጃውይጠቅሳል፡፡ አዳዲሶቹስኳርፋብሪካዎችማለትምኩራዝ፣የጣናበለስእናወልቃትየመስኖመሰረተልማትግንባታ፣የመሬትዝግጅትናየሸንኮራአገዳተከላ፣የፋብሪካናየመኖሪያቤትግንባታዎችእየተከናወኑቢሆንምአፈጻጸማቸውበዝቅተኛደረጃላይእንደሚገኝተመልክቷል፡፡ በዚህምምክንያትፕሮጀክቶቹየዕድገትናየትራንስፎርሜሽንእቅዱ በሚጠናቀቅበትበቀጣይአንድኣመትጊዜያትእንደማይደርሱከወዲሁተረጋግጦአል፡፡ በአንድወቅትየስኳርኮርፖሬሽንዳይሬክተርየነበሩትአቶአባይጸሐዬየስኳርፋብሪካዎቹበዘርፉልምድ ባለመኖሩምክንያትየማስፈጸምአቅምማጋጠሙንአምነው  “እየተማርንበመስራትላይነን” በማለትበፓርላማመድረክያደረጉትንግግርበሃገርሐብትመቀለድነውበሚልከፍተኛትችትአስከትሎባቸውእንደነበርየሚታወስነው፡፡ በሌላ ዜና ደግሞ በውጭሃገርካሉኢትዮጵያዊያንእናመንግስታዊያልሆኑድርጅቶችአማካይነትወደ ሃገርውስጥየሚገባውሃዋላየወጪንግዱንገቢእየተገዳደረውመሆኑንከብሔራዊባንክየተገኘመረጃጠቆመ፡፡ እየተገባደደባለውየኢትዮጵያዊያን 2006 በጀትዓመትዘጠኝወራትከሸቀጦችኤክስፖርት 2  ቢሊየንዶላርሲገኝከግልሃዋላምተቀራራቢበሆነመልኩ 2 ቢሊየንዶላርተገኝቷል፡፡ አምናበ2005 በጀትዓመትሃገሪቱከሸቀጦችንግድ 3 ቢሊየንየአሜሪካንዶላርስታገኝከግልሃዋላደግሞ 4ቢሊየንዶላርማግኘትዋንመረጃውንይጠቅሳል፡፡ የባንኩመረጃእንደሚያሳየውበውጪአገርየሚኖሩኢትዮጵያዊንለወገኖቻቸውንናለተለያዩስራዎችማስኬጃወደሃገርውስጥየሚያስገቡትዶላርበዓመትእስከ 20 ...

Read More »

በኬንያ የሽብር ጥቃት ፈጽመዋል የተባሉ በርካታ ሰዎች ታሰሩ

ሰኔ ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቢቢሲ እንደዘገበው በላሙ የወደብ ዳርቻ ሰሞኑን የተፈጸመው ጥቃት የ60 ሰዎችን ህይወት አጥፍቷል። ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጥቃቱን የፈጸመው አልሸባብ አለመሆኑን ገልጸው ነበር። ጥቃቱ በአልሸባብ እንደተፈጸመ ተደርጎ መረጃውን ያሰራጨውን ሰው መያዙም ተገልጿል። ግድያው ከጎሳ ፖለቲካ ጋር የተያያዘ እንደሆነ የአገሪቱ መንግስት ገልጿል። ሰሞኑን በተፈጸመው ጥቃት ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪ 12 ሴቶችም ታፍነው ተወስደዋል። ታፍነው የተወሰዱት ሴቶች የት እንደገቡ ...

Read More »

የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉት ዜጎች ለክስ የሚያበቃ በደል አልደረሰባቸውም አለ።

ሰኔ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት የመሰረቱት ክስ በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት 8ኛ ፍትሃ ብሄር ምድብ በዋለው ችሎት የታየ ሲሆን ፣ በቀረበው ክስ ላይ የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴርና የቤንሻንጉል ክልል መንግስት መልስ ሰጥተዋል። ከሳሾች ለበርካታ አመታት ከኖሩበት ቀየ በህገወጥ መንገድ በመፈናቀላቸው ሃብትና ንብረታቸውን ማጣታቸውን በጠበቃቸው አማካኝነት ተናግረዋል። የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በበኩሉ ከሳሾቹ ቤት ንብረት ...

Read More »

ከቁጫ የአገር ሽማግሌዎች በድጋሜ ለአቤቱታ ሊሄዱ ነው።

ሰኔ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በቁጫ ወረዳ በቅርቡ ከተነሳው የመልካም አስተዳደር ፣ የማንነትና የፍትህ ጥያቄ ጋር በተያያዘ ፍትህ አጥተው ያለፉትን ስምንት ወራት በእስር ቤት ካሳለፉ ትመካከል የ14 የቤተሰብ አባላት አስተዳዳሪ የሆኑት የ39 ዓመቱ አቶ ሻልሼሸዋ ከሞቱና የሌሎችም እስረኞች ህይወት አደጋ ላይ በመውደቁ እንዲሁም በአካባቢው ድጋሜ ግጭት ይነሳል የሚል ስጋት በመፍጠሩ 4 የአገር ሽማግሌዎች ጉዳዩን ለፌደራሉ መንግስት በድጋሜ ...

Read More »

የጋዝጊብላ ነዋሪዎች ኢህአዴግ ክዶናል ሲሉ ተናገሩ።

ሰኔ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ከትግራይ ህዝብ በመቀጠል ኢህአዴግ ወደ ስልጣን እንዲመጣ ከፍተኛ የህይወት መስዋትነት የከፈለው የሰቆጣና አካባቢዋ ነዋሪዎች ቢሆኑም፣ ኢህአዴግ አዲስ አበባ ከገባ ጀምሮ እንደረሳቸው ገልጸዋል። ከሶቆጣ 48 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘዋ ጋዝጊብላ ወረዳ የሚኖሩ የቀድሞ ታጋዮች ለኢሳት እንደገለጹት፣ ለኢህአዴግ ልጁን ያልገበረ ሰው ባይኖርም፣ ባለስልጣናቱ ግን ውለታቸውን መርሳታቸውን ተናግረዋል። ከሰቆጣ ላሊበላ የህዝብ ትራንስፖርት አለመኖሩን ፣ ከአዲስ ...

Read More »

በኬንያ በርካታ ሴቶች ታፍነው ተወሰዱ።

ሰኔ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አልሸባብ እንደፈጸመው በተጠቀሰው ጥቃት 48 ሰዎች በተገደሉ ማግስት፣ ሌሎች ተጨማሪ 12 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን፣ ከ12 ያላነሱ ሴቶችም በታጣቂዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። ምፔኬቲኒ እየተባለ በሚጠራው የወደብ ከተማ ላይ የደረሰውን ተከታታይ ጥቃት አልሸባብ እንደፈጸመው እየተዘገበ ባለበት ወቅት፣ የአገሪቱ መሪ ኡሁሩ ኬንያታ ፣ ጥቃቱ በራሳቸው ባለስልጣናት የተቀነባበረና ከጎሳ ጋር የተያያዘ መሆኑን በመግለጽ፣ አልሸባብ ፈጸምኩ የሚለውን ጥቃት ...

Read More »

ባግዳድ በሱኒ ታጣቂዎች እጅ ልትወድቅ መቃረቡን ተከትሎ አሜሪካ የኢምባሲ ሰራተኞችን እያስወጣች ነው።

ሰኔ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባልታሰበ ቅጽበት የተለያዩ የሰሜን ኢራቅ ከተሞችን እየተቆጣጠሩ የመጡት የሱኒ ኢስላሚክ ታጣቂዎች ፣ ዋና ከተማዋን ባግዳድን ለመያዝ በቅርብ እርቀት እየተፋለሙ ሲሆን፣ አሜሪካ የኢምባሲ ሰራተኞቹዋን ለማሸሽ ሽፋን የሚሰጡ ከ250 በላይ የጦር ሰራዊቷን መላኩዋ ታውቋል። የእግረኛ ሰራዊት ለመላክ እንደማትሻ ያስታወቀችው አሜሪካ፣ በኢራቅ ላይ ስለምትወስደው እርምጃ ውሳኔ ላይ አልደረሰችም። እስላሚክ ታጣቂዎቹ ባግዳድን ከተቆጣጠሩ ከሺያ ታጣቂዎች ጋር ደም አፋሳሽ ...

Read More »