.የኢሳት አማርኛ ዜና

ኢትዮጵያ የጋዜጠኞችን መብት በማክበር ረገድ 150ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች

(ኢሳት ዲሲ–ሚያዚያ 17/2010) ኢትዮጵያ የጋዜጠኞችን መብት በማክበር ረገድ ከአለም 180 ሀገራት ጋር ስትነጻጸር በ150ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ድንበር የለሽ የሪፖርተሮች ቡድን አመለከተ። ድንበር የለሽ የሪፖርተሮች ቡድን የተባለ አለም አቀፍ ተቋም የየሃገራቱን የጋዜጠኞች መብት አከባበር አስመልክቶ ባወጣው የግምገማ ሪፖርት እንደገለጸው ኢትዮጵያ በአሸባሪነት ሰበብ ጋዜጠኞችን በማሳደድ የከፋ ርምጃ ትወስዳለች። ኢትዮጵያ የጋዜጠኞችን መብት አከባበር በተመለከተ ከአመት አመት ሁኔታውን ከማሻሻል ይልቅ የባሰ ርምጃ እየወሰደች ...

Read More »

የአብዲ ዒሌና የሽንሌ ዞን የሀገር ሽማግሌዎች ድርድር ያለውጤት ተበተነ

(ኢሳት ዲሲ–ሚያዚያ 17/2010) የአብዲ ዒሌና የሽንሌ ዞን የሀገር ሽማግሌዎች ድርድር ያለውጤት ተበተነ:: አንድ ሳምንት የሞላውን ተቃውሞ ለማስቆም በአብዲ ዒሌ በኩል ግፊት የተደረገበት ድርድር የከሸፈው በእስር ላይ የሚገኙ ወጣቶች እንደማይፈቱ በመገለፁ ነው:: የክልሉን ምክትል ፕሬዝዳንት የላከው አብዲ ዒሌ በኮማንድ ፖስቱ የታሰሩ በመሆናቸው ልንፈታቸው አንችልም የሚል መልስ ለሽማግሌዎቹ ተነግሯቸል :: ይህ በእንዲህ እንዳለም በሶማሌ ክልል ሽንሌ ዞን የተጀመረው ተቃውሞ መቀጠሉ ታውቋል:: ድርድሩ ...

Read More »

የተመድ የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ከእስር ከተፈቱት ታዋቂ ሰዎችና ከፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ጋር ተነጋገሩ

የተመድ የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ከእስር ከተፈቱት ታዋቂ ሰዎችና ከፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ጋር ተነጋገሩ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 17 ቀን 2010 ዓ/ም) የተመድ የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን ከተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጓቾችና ጋዜጠኞች ጋር ተወያይተዋል። ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ ያሉት ኮሚሽነሩ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ዙሪያ እና አገሪቱ መውሰድ ስለሚገባት እርምጃ አስተያቶችን ሰብስበዋል። በገዥው ፓርቲ ባለስልጣናት ወደ ...

Read More »

በሺኒሌ ዞን ያለውን ተቃውሞ ተከትሎ ዜጎች በገፍ እየታሰሩ ነው

በሺኒሌ ዞን ያለውን ተቃውሞ ተከትሎ ዜጎች በገፍ እየታሰሩ ነው (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 17 ቀን 2010 ዓ/ም) በረባራት እየተባሉ የሚጠሩ ወጣቶች በአቶ አብዲ ኢሌ አገዛዝ በመማረር የጀመሩትን ተቃውሞ ተከትሎ በርካታ ወጣቶች ተይዘው ታስረዋል። በርካታ ወጣቶች በተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥ እንደሚገኙ የገለጹት ምንጮች፣ የእስር ዘመቻው ተጠናክሮ በመቀጠሉ አካባቢው በውጥረት እንደሚሞላ አድርጎታል። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት በአካባባቢው በማሰማራት ተቃውሞውን ለማፈን ጥረት መደረጉን የአካባቢው ...

Read More »

“አገራችን በጥሩ እጅ ላይ ወድቃለች” ሲሉ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ተናገሩ

“አገራችን በጥሩ እጅ ላይ ወድቃለች” ሲሉ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ተናገሩ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 17 ቀን 2010 ዓ/ም) የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር ይህን የተናገሩት በቤተመንግስት የመሸኛ ዝግጅት በተደረገላቸው ወቅት ነው። አቶ ሃይለማርያም ለአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ያላቸውን አድናቆት ከገለጹ በሁዋላ በአገሪቱ እየነፈሰ ያለው የለውጥ ንፋስ ህዝቡ በሚፈልገው መሰረት እንዲከናወን ከፍተኛ ትግል ያስፈልጋል ብለዋል። “በአሁኑ ወቅት የለውጥ ንፋስ እየነፈሰ ነው፡፡ ለውጡ የሁላችንንም ፍላጎት ያማከለ እንዲሆን ልንረባረብ ...

Read More »

በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዝርፊያ እየተፈጸመባቸው ነው

በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዝርፊያ እየተፈጸመባቸው ነው (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 17 ቀን 2010 ዓ/ም) ኢትዮጵያኑ እንዳሉት የአገሪቱ ዜጎች የፖለቲካ ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ወደ አደባባይ ከወጡ በሁዋላ የስደተኞችን ንብረቶች በመዝረፍ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል። ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን እንደገለጹት፣ በዝርፊያው በርካታ ኢትዮጵያውያን ሃብትና ንብረታቸውን አጥተዋል። በሌላ በኩል ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው 26 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሞዛንቢክ ውስጥ ተያዙ በሕገወጥ መንገድ ሞዛምቢክን አቆራርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ...

Read More »

በካናዳ ቶሮንቶ አንድ እቃ ጫኝ መለስተኛ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ 10 አካል ጉዳተኞች ተገደሉ

(ኢሳት ዲሲ–ሚያዚያ 15/2010) በካናዳ ቶሮንቶ አንድ እቃ ጫኝ መለስተኛ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ 10 አካል ጉዳተኞችን ሲገድል 15 ማቁሰሉ ተሰማ። የካናዳ ፖሊስ አደጋው ሆን ተብሎ ነው የተፈጸመው ቢልም ምክንያቱ ምን እንደሆነ ግን ማወቅ አልተቻለም ሲል ገልጿል። የአደጋው ፈጻሚ የ25 አመቱ አሌክ ሚናሲያ አደጋውን ካደረሰ በኋላ ለመሸሽ ቢሞክርም ብዙም ሳይርቅ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል። በካናዳ ቶሮንቶ ዮንጌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው ...

Read More »

አቶ ጌታቸው አምባዬ ከስልጣን የተነሱት በሙስናና እስረኞችን አልፈታም በማለታቸው ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሚያዚያ 16/2010)በኢትዮጵያ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ሆነው የሰሩት አቶ ጌታቸው አምባዬ ከስልጣን የተነሱት ከሙስናና ከሕወሃት ጋር ባላቸው ቅርበት እስረኞችን አልፈታም እያሉ በማስቸገራቸው መሆኑን የኢሳት ምንጮች ገለጹ። አቶ ጌታቸው አምባዬ በተለይም የዋልድባ መነኮሳትን ላለመልቀቅ በማቅማማታቸው ከእስር ሳይፈቱ እንዲዘገዩ አድርገዋል ተብሏል። የቀድሞው አቃቤ ሕግ አቶ ጌታቸው አምባዬ በነባሩም ይሁን በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር መነኮሳቱን እንዲፈቱ ተጠይቀው እምቢተኛ ሆነው መቆየታቸውንም ለማወቅ ...

Read More »

በአማራ ክልል ባሉ ከተሞች የነዳጅ እጥረት ተከሰተ

(ኢሳት ዲሲ–ሚያዚያ 16/2010) በአማራ ክልል ባሉ ከተሞች ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት መከሰቱ ተነገረ። በዚህም ሳቢያ በየአካባቢዎቹ የትራንስፖርት መስተጓጎል ተፈጥሯል። የነዳጅ እጥረቱ መንስኤ ምን እንደሆነ በውል ባይታወቅም ችግሩ ከውጭ ምንዛሬ እጥረት ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል የአካባቢው ምንጮች ይናገራሉ። በባህርዳር ፣ ወረታ ፣ጎንደር ፣ ደብረታቦር ፣ ወልዲያ ፣ ደብረማርቆስ ፣ ኮሶበርና መሰል ከተሞች ቤንዚንና ናፍጣ በነዳጅ ማደያዎች ባለመኖሩ የትራንስፖርት ችግር ተፈጥሯል። የኢሳት ምንጮች ...

Read More »

በኢትዮጵያ 8 ሚሊየን ሕዝብ አስቸኳይ እርዳታ ካላገኘ ሕይወቱ አደጋ ላይ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሚያዚያ 16/2010) በኢትዮጵያ የምግብ እርዳታ የሚፈልጉ 8 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ እርዳታ ካላገኙ ሕይወታቸው አደጋ ላይ መሆኑ ተነገረ። የአለም የምግብ ፕሮግራም ይፋ ባደረገው የአስቸኳይ ጊዜ ሪፖርት እንደተመለከተው 1 ነጥብ 8 ሚሊየን የሶማሌ ክልል ነዋሪ ኢትዮጵያውያን በሕይወት ለመቆየት አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። የአለም የምግብ ፕሮግራም ይፋ ባደረገው የአደጋ ጊዜ ሪፖርት በዚህ በተያዘው የምዕራባውያኑ 2018 ዓመተ ምህረት 7 ነጥብ 9 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ...

Read More »