(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2010)ለሶስት ቀናት በማህበራዊ መድረኮች የተጠራውና አንዳርጋቸው ጽጌ ይፈታ በሚል የተደረገው ዘመቻ የተሳካ እንደነበር አስተባባሪዎቹ ገለጹ። በሀገር ውስጥ በሚገኙ አክቲቪስቶች የተጠራው ዘመቻ በሶስት ቀናቱ ቆይታ ስለአንዳርጋቸው ጽጌ የተላለፉት መልዕክቶችና የህዝቡ ተሳትፎ ከተጠበቀው በላይ እንደሆነም ገልጸዋል። ዘመቻው ወደፊትም በተለያዩ ፕሮግራሞች የሚቀጥል መሆኑንም አስታውቀዋል። የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ በሰማያዊ ፓርቲ ጽሕፈት ቤት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን የተመለከተ ውይይት መዘጋጀቱንም የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
በቂሊንጦ ከችሎት የተመለሱ 11 እስረኞች ጨለማ ክፍል ውስጥ እንዲዘጋባቸው ተደረገ
(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2010) በቂሊንጦ ወህኒ ቤት ቃጠሎ በማስነሳት ግድያ ፈጽመዋል በሚል ክስ ከተመሰረተባቸው 30 ያህል እስረኞች አስራ አንዱ ችሎት ውለው ሲመለሱ ጨለማ ክፍል ውስጥ እንዲዘጋባቸው መደረጉ ተገለጸ። ከትላንት በስቲያ ፍርድ ቤት ቀርበው የተከላከሉ ብይን የተላለፈባቸው እስረኞች ዛሬ ወደ ጨለማ ቤት ሲወሰዱ በነበረው ተቃውሞ በግቢው ውስጥ ውጥረት መንገሱም ተሰምቷል። ማክሰኞ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ከቀረቡት ተከሳሾች 8ቱ በነጻ ...
Read More »የሜድሮክ በለገደንቢ የወርቅ ማውጣት ፈቃድ ታገደ
(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2010)ለሜድሮክ ኢትዮጵያ የወርቅ ማዕድን ማውጣት ፈቃድ መታደሱን በመቃወም የተካሄደውን መጠነ ሰፊ የሕዝብ እንቅስቃሴ ተከትሎ የሜድሮክ ፈቃድ መታገዱን መንግስት ይፋ አድርጓል። የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር ትላንት እንዳስታወቀው ተጨማሪ ጥናት ተካሂዶ ጉዳዩ እልባት እስኪያገኝ ድረስ ሜድሮክ ወርቅ የማምረት ስራውን እንዲያቋርጥ ተደርጓል ተብሏል። ባለፉት 20 አመታት በለገደምቢ ወርቅ ሲያመርት የቆየው የሼህ መሃመድ አላሙዲን ንብረት የሆነው ሜድሮክ የወርቅ ማምረቻ በቅርቡ ለተጨማሪ 10 አመታት ...
Read More »ግሎባል አሊያንስ ከቤንሻንጉል ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ8 መቶ ሺህ ብር በላይ እረዳ
(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2010) አለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን/ግሎባል አሊያንስ/ ከቤንሻንጉል ክልል ለተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆች ከ8 መቶ ሺህ ብር በላይ እርዳታ ሰጠ። በአርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ የሚመራው ግሎባል አሊያንስ ለተፈናቀሉት የአማራ ተወላጆች የላከውን ገንዘብ ለብርድልብስና አልባሳት እንዲሁም ለእለት ምግባቸው እንደሚያውሉት ተረጂዎቹ ለኢሳት ገልጸዋል። ተፈናቃዮች በግሎባል አሊያንስ ወገናዊነት ልባቸው እንደተነካ በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል። በባህር ዳር ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የተጠለሉት ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈናቀሉት የአማራ ...
Read More »በጉጂና በጌዲዮ ብሄረሰቦች ግጭት የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 200ሺህ ደረሰ
(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2010)በጉጂና በጌዲዮ ብሄረሰቦች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 200ሺህ መድረሱን የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ። የድርጅቱ የሰብዓዊ እርዳታ ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኦቻ ባወጣው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ባለፈው ወር መጀመሪያ ላይ በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈጠረው ግጭት ካፈናቀለው ህዝብ በተጨማሪ በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል። ጽሕፈት ቤቱ ለተጎጂዎች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም አስታውቋል። በግጭቱ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን መገለጹ ...
Read More »የአማራ ተወላጆች እንዲገደሉና እንዲፈናቀሉ ያደረገው የቦሎ ዴዴሳ ቀበሌ መስተዳድር መሆኑ ታወቀ
(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2010) በቤንሻንጉል ክልል ይኖሩ የነበሩትን የአማራ ተወላጆች እንዲገደሉና እንዲፈናቀሉ ያደረገው በካማሽ ዞን የቦሎ ዴዴሳ ቀበሌ መስተዳድር መሆኑን የሚያረጋግጥ የደብዳቤ ሰነድ ይፋ ሆነ። የቦሎ ዴዴሳ ቀበሌ መስተዳድር ለአማራ ተወላጆች በሚል በጻፈው ደብዳቤ እስከ መጋቢት 30 ወይንም ሚያዚያ 10/2010 ድረስ አካባቢውን ለቃችሁ ካልወጣችሁ ተገዳችሁ ትለቃላችሁ የሚል ማስጠንቀቂያ መጋቢት 30/2010 መጻፉን ለማረጋገጥ ተችሏል። ደብዳቤው የአማራ ተወላጆች ሃብትና ንብረታቸውን ሸጠው እንዲወጡ ማሳሰቢያ ...
Read More »የአማራተ ወላጆች ከቡሎ ዴዴሳ ቀበሌ እንዲወጡ የታዘዙበት ደብዳቤ ከተጻፈ ጀምሮ ሁሉም የአማራተወላጆች አካባቢውን ለቀው መውጣታቸውን ተፈናቃዮች ገለጹ
የአማራተ ወላጆች ከቡሎ ዴዴሳ ቀበሌ እንዲወጡ የታዘዙበት ደብዳቤ ከተጻፈ ጀምሮ ሁሉም የአማራተወላጆች አካባቢውን ለቀው መውጣታቸውን ተፈናቃዮች ገለጹ (ኢሳት ዜና ግንቦት 02 ቀን 2010 ዓ/ም) ንጉሴ ጀርሞሳ በተባለው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የቦሎዴዴሳ ሊ/መንበር የተጻፈው ደብዳቤ “የአማራ ተወላጆች በሙሉ እስከ መጋቢት 30 ቀን 2010ዓም ወይም እስከ ሚያዚያ 10/2010 ዓም ሃብታቸውንና ንብረታቸውን ሽጠው ወይም አርደው እንዲወጡ” ያዛል። ይህንን ትዕዛዝ አክብረው የማይወጡ የአማራ ተወላጆች ...
Read More »ህወሃት ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠርበትን እቅድ ለመንደፍ መቀሌ ከትሟል
ህወሃት ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠርበትን እቅድ ለመንደፍ መቀሌ ከትሟል (ኢሳት ዜና ግንቦት 02 ቀን 2010 ዓ/ም) የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ተከታታይ የሆኑ ህዝባዊ ተቃውሞዎች የበዙበት ህወሃት፣ ሙሉ ስልጣኑን መልሶ የሚቆጣጠርበትን ስልት ለመንደፍ መቀሌ ላይ ከትሞ ጥናት እያደረገ ነው ። ህዋሃት እራሱን ከአንዳንድ የፌደራል መንግስት የስልጣን ቦታዎች በማራቅና ህወሃት የሌለበት በማስመሰል እንዲሁም የፌደራል መንግስትን የማስፈጸም አቅም በተለያዩ እንቅፋቶች በመክበብ እና በማደነቃቀፍ ህወሃት ...
Read More »የህሊና እስረኞች ድብደባ ተፈጸመባቸው
የህሊና እስረኞች ድብደባ ተፈጸመባቸው (ኢሳት ዜና ግንቦት 02 ቀን 2010 ዓ/ም) በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ የክስ መዝገብ ተከሰው ከሚገኙት እስረኞች መካከል የተወሰኑ እስረኞች ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ታውቋል። ሚያዚያ 30 ቀን 2010 ዓም በዋለው ችሎት ተከላከሉ የተባሉት ተከሳሾች ያሰሙትን ተቃውሞ ተከትሎ የእስር ቤት ፖሊሶች በተከሳሾች ላይ ድብደባ የፈጸሙባቸው ሲሆን፣ በድብደባው ብዛት አንዳንዶች አካላቸው ተጎድቷል። 11 ተከሳሾች ደግሞ በቅጣት መልክ ጨለማ ቤት እንዲታሰሩ ...
Read More »አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሲታወስ የሚል የውይይት መድረክ አዲስ አበባ ላይ ተዘጋጀ
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሲታወስ የሚል የውይይት መድረክ አዲስ አበባ ላይ ተዘጋጀ (ኢሳት ዜና ግንቦት 02 ቀን 2010 ዓ/ም) ሰማያዊፓርቲ “አንዳርጋቸው ጽጌ ሲታወስ” በሚልርዕስ ግንቦት4 ቀን 2010ዓም የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። በውይይቱ ላይ መምህርትና ጋዜጠኛ መስከረም አበራ በእንግድነት ተጋብዛለች ። ውይይቱ አምባሳደር ሲኒማ አካባቢ በሚገኘው የሰማያዊፓርቲ ጽ/ቤት ውስጥ ከጠዋቱ 8፡30-11፡00 ሰዓት ይካሄዳል። አቶ አንዳርጋቸው እንዲፈታ የሚጠይቀው የ3 ቀናት የማህበራዊ ዘመቻ በተሳካ ሁኔታ ...
Read More »