z-Advert

የአሜሪካ የኢሚግሬሽንና ጉምሩክ ባለስልጣን ርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱን አስታወቀ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 14/2010) የስራ ፈቃድ ሳይኖራቸው በሆቴሎችና በልዩ ልዩ ቦታዎች አገልግሎት በሚሰጡ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የአሜሪካ የኢሚግሬሽንና ጉምሩክ ባለስልጣን ርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱን አስታወቀ። በዋናነት በአሰሪዎቹ ላይ ያነጣጠረውና ተቀጣሪዎቹንም የማይተወው ርምጃ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር በማዋል ክስ መመስረትንም ይጨምራል። ተቀጣሪዎቹ ደግሞ በሌላ ወንጀል የሚፈለጉ ካልሆነ በቀር ከአሜሪካ እንዲባረሩ ይደረጋል ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ። በግዙፎቹ የንግድ ተቋማት ላይ የተነጣጠረ ነው የተባለው የአሜሪካ የኢሚግሬሽንና ...

Read More »

በሞያሌ የተሰወሩትን ወታደሮች ፍለጋ ቀጥሏል

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 13/2010)በሞያሌ ከትላንት በስቲያ የተሰወሩትን ወታደሮች ለመፈለግ የወጣው አሳሽ ቡዳን ዛሬም ፍለጋውን መቀጠሉ ተገለጸ። ከ30በላይ ወታደሮች ከነሙሉ ትጥቃቸው ከተሰወሩ በኋላ በ10ኛው ክ/ጦር ባሉ ወታደሮች ዘንድ ውጥረት ነግሷል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የሬዲዮ መገናኛ ኦፕሬተር መታሰሩን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ወታደሮቹ ከተሰወሩ በኋላ በክ/ጦሩ የአማራና የኦሮሞ ተወላጅ በሆኑ የሰራዊቱ አባላት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑንንም ለማወቅ ተችሏል። ከትላንት በስቲያ ሰኞ ነው። በ10ኛ ...

Read More »

የዚምባቡዌ አዲስ ፕሬዝዳንት አርብ ቃለ ማሃላ ይፈጽማሉ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 13/2010)የዚምባቡዌ አዲስ ፕሬዝዳንት የፊታችን አርብ ቃለ ማሃላ እንደሚፈጽሙ ታወቀ። ሀገሪቱን ለ37 አመታት የገዙት ሮበርት ሙጋቤን ከስልጣን መልቀቅ ተከትሎ የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ኤመርሰን ናንጋግዋን በፕሬዝዳንትነት ለመሾም ዝግጅት እየተደረገ ነው። ዚምባቡዌን ለ37 አመታት የመሩት ሮበርት ሙጋቤ ትላንት ከስልጣን መልቀቅን ተከትሎ የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑትና ከሁለት ሳምንት በፊት በሙጋቤ በሙጋቤ ከስልጣኝ ተወግደው የነበሩት ኤምርሰን ናንጋግዋ በፕሬዝዳንትነት እንደሚሾሙ ከሀገሪቱ የሚወጡ መረጃዎች ...

Read More »

መሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለመንግስት ትላልቅ ፕሮጀክቶች በብቸኝነት ሲሚንቶ እያቀረብኩ ነው አለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 13/2010)መሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለመንግስት ትላልቅ ፕሮጀክቶች በብቸኝነት ሲሚንቶ ማቅረብ የቻልኩት ልዩ ሲሚንቶዎችን በብቸኝነት የማመርት በመሆኔ ነው አለ። የኤፈርት ኩባንያ አካል የሆነው መሶቦ ሲሚንቶ ለግዙፍ ፕሮጀክቶቹ በብቸኝነት እንዲያቀርብ የተደረገው ግዙፉ የሙገር ሲሞንቶ ፋብሪካ በህወሃት ስርዓት በተለያየ መንገድ የማምረት አቅሙ እንዲዳከም ከተደረገ በኋላ መሆኑ ይታወቃል። በህወሃት ንብረትነት የሚተዳደረው ኤፈርት ኩባንያ አካል የሆነው የመሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ በ2009 ብቻ በኢትዮጵያ ለተከናወኑ የፕሮጀክት ...

Read More »

ዘርአይ አስገዶምን ዘረኛና ጎጠኛ ሲሉ የፓርላማ አባላት አወገዙ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 13/2010) የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዘርአይ አስገዶምን ዘረኛና ጎጠኛ ሲሉ የፓርላማ አባላት አወገዙ። አባላቱ ኢሕአዴግን ተጠልሎ ዘረኝነትን በኦፊሴላዊ ደረጃ ማራመድ፣ስልጣንን ማሳነስና የስም ማጥፋት ዘመቻ መክፈት ተጠያቂ ያደርጋል ብለዋል። የኮሚኒኬሽን ጽሕፈት ቤትም ሆነ ሚኒስትሩ የሚወክሉት መንግስትን የሚያንጸባርቁትም የመንግስትን አቋም ነው ብለዋል አባላቱ። የመንግስት ኮሚኒኬሽኝ ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ህዳር 11/2010 ለፓርላማው የባህል፣ ቱሪዝምና መገናኛ ብዙሃን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ...

Read More »

የፌደራል ፖሊስ የሰሜን ምዕራብ አዛዥ ተገደሉ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 13/2010) የፌደራል ፖሊስ የሰሜን ምዕራብ አዛዥ ትላንት ምሽት በባህር ዳር መገደላቸው ተገለጸ። ኮማንደር ደሳለኝ ልጃለም ማንነታቸው ባልታወቁ ሃይሎች በመኖሪያ ቤታቸው ግቢ ውስጥ የተገደሉት ትላንት ምሽት አምስት ሰዓት ላይ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል። ኮማንደር ደሳለኝ በባህር ዳር ከተማ በተካሄዱ ህዝባዊ ተቃውሞዎች ላይ ከተገደሉት ወጣቶች ጋር በተያያዘ ስማቸው የሚጠቀስ አዛዥ መሆናቸው ታውቋል። ከህወሀት የተሰጠውን መመሪያ በማስፈጸምም ለበርካቶች ግድያ ስቃይ ተጠያቂ እንደሆኑም ...

Read More »

የእርስ በርስ ግጭት ለመፍጠር የሚደረገውን እንቅስቃሴ ህብረተሰቡ እንዲያከሽፈው ተጠየቀ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 13/2010)በባሌ ጎባ በህወሃት መንግስት አማካኝነት የእርስ በርስ ግጭት ለመፍጠር የሚደረገውን እንቅስቃሴ ህብረተሰቡ እንዲያከሽፈው ተጠየቀ። የጎባ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ የህዝቡን ተቃውሞ በማሳነስ ያደረጉት ንግግር ቁጣን ቀስቅሷል። ምክትል አስተዳዳሪዋ ጥቃት እንዳይደርስባቸው በመንግስት ወታደሮች ጥበቃ እየተደረገላቸው መሆኑም ታውቋል። ይህን የህዝብ ቁጣ ለማስቀየስ በህዝቡ መሀል ሃይማኖትንና ብሄርን መነሻ ያደረገ ግጭት ለመቀስቀስ በመንግስት በኩል እንቅስቃሴ መጀመሩን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ካለፈው ሰኞ ህዳር 11 ...

Read More »

ሮበርት ሙጋቤ ስልጣናቸውን ለቀቁ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 12/2010)የዚምባቡዌው ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን ለቀቁ። ፕሬዝዳንቱ የመልቀቂያ ደብዳቤያቸውን ያቀረቡት የሀገራቸው የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት እሳቸውን ከመንበረ ስልጣናቸው ለማውረድ ባሉበት ሰአት መሆኑ ታውቋል። በዚምባቡዌ ለ37 አመታት በስልጣን ላይ የቆዩት ሮበርት ገብርኤል ሙጋቤ ዛሬ በፈቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸውን ከሮይተርስ ዘገባ መረዳት ተችሏል። በዚምባቡዌ የሕግ አዉጪ ምክር ቤት ፕሬዝዳንቱን በሕግ ለመጠየቅና ለመክሰስ እየተካሄደ ያለውን የፖርላማ ስርአት አቋርጠው አፈ ጉባኤው ...

Read More »

ኢትዮጵያውያን አደገኛ ወንጀል በመፈጸም የተሰወሩ ግለሰቦችን መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ የዋሽንግተን ዲሲ ፖሊስ ጠየቀ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 12/2010)በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች ዜጎች በዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ አደገኛ ወንጀል በመፈጸም የተሰወሩ ግለሰቦችን በተመለከተ መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀረበ። የዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ፖሊስ ዲፓርትመንት ለኢሳት በላከው መግለጫ በመሳሪያ የተደገፈ ጥቃት ፈጽመው የተሰወሩ ግለሰቦችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል። በቅርቡ ህዳር 6/2017 ከምሽቱ 8 ሰዓት ከ20 ላይ በጆርጂያ ጎዳና በ5 ሺ አራት መቶ አድራሻ ...

Read More »

ሜቴክ የተጀመሩ የስኳር ፕሮጀክቶችን ያላጠናቀቁት የአቅም ችግር ስላለብኝ ነው አለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 12/2010) የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን/ሜቴክ/ የተጀመሩ የስኳር ፕሮጀክቶችን ያላጠናቀቁት የአቅም ችግር ስላለብኝ ነው አለ። የተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ የሜቴክ ውጫዊ ምክንያቶች በዝተዋል እኔም በሜቴክ ጉዳይ ተሰላችቻለሁ ሲል ተናግሯል። የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን/ሜቴክ/ በየጊዜው በግዴታም ይሁን በማስገደድ አልፎ አልፎም በውይይት የሚወስዳቸው ፕሮጀክቶች ብዛት በርካታ ናቸው። ነገር ግን ሜቴክ እንደሚወራለትና እሱም እሰራቸዋለሁ ...

Read More »