በብራሰልስ የሚካሄደው የኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ ቅድመ ዝግጅት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን ዘጋጆች ገለጹ

የካቲት ፩፮ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-እውቁ የሰብአዊ መብት ተሟጋች አርቲስት ታማኝ በየነ የሚሳተፍበት በቤልጂየም ብራሰልስ የኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በጥሩ ሁኔታ ሲካሄድ መሰንበቱን የዝግጅቱ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ገበየሁ ደስታ  ለኢሳት ገልጸዋል። በቤልጂየም የኢትዮጵያውያን ኮሚቴ ማህበር ከኢሳት የቀረበለትን የትብብር ጥያቄ ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆኑ እንዳሳዘናቸው  አቶ ገበየሁ አልሸሸጉም ። የኢሳት የገቢ መሳባሰቢያ አዘጋጆች ለማህበሩ ያቀረቡት ጥያቄ ፣ የኮሚኒቲውን ኔት ...

Read More »

ካኤልም- ኤር ፍራንስ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርገውን በረራ ሰረዘ

የካቲት ፩፮ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኔዘርላንድስ አየር መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርገውን በረራ የሰረዘው አትራፊ ባለመሆኑ ነው ብሎአል። ድርጅቱ ለሪፖርተር እንደገለጠው ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርገውን በረራ ከተለያዩ አየር መንገዶች በገጠመው ውድድር እንዲሁም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በማሳየቱ ለመሰረዝ ተገዷል። “ወደ ኢትዮጵያ የምናደርገው በረራ አትራፊ አይደለም” ያሉት የካኤል ኤም የኢትዮጵያና የሱዳን ወኪል ሚ/ር ዲክ ቫን ኒወንሀውዘን፣ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉትን በረራ ሸሪክ ...

Read More »

በአጋሮ በርካታ ሙስሊሞች መደብደባቸው ታወቀ

የካቲት ፩፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የጁመአን ስግደት ተከትሎ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ድምጻችን ይሰማ በማለት ተቃውሞአቸውን ለመግለጽ ቢሞክሩም የፌደራል ፖሊስ አባላት የሀይል እርምጃ ወስደዋል። በርካቶች መታሰራቸውን፣ መደብደባቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል:: ከፍተኛ ተቃውሞ ከታየባቸው ከተሞች መካከል ሻሸመኔ አንዱ ሲሆን፣ በርካቶች በ04 መስጊድ ተገኝተው ድምጻችን ይሰማ መሪዎቻችን ይፈቱ ማለታቸውን ለማወቅ ተችሎአል። ተመሳሳይ ተቃውሞዎች በበደሌ፣ መቱና ድሬዳዋ መካሄዳቸውን ለማወቅ ተችሎአል። የኢትዮጵያ ...

Read More »

ሰመጉ የተላለፈው ዘጋቢ ፊልም የተከሰሱ ሰዎችን ሕገመንግስታዊ መብት የጣሰ ነው ባወጣው መግለጫ አስታወቀ

የካቲት ፩፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ሰመጉ በዚሁ መግለጫው በፌዴራል ፖሊስና በብሄራዊ ደህንነት እና ጸጥታ ባለስልጣን ተዘጋጅቶ በኢቲቪ እንዲቀርብ የተደረገው ፊልም ተጠርጣሪዎቹ በሕገመንግስቱ መሰረት በተከሰሱበት ወንጀል ከፍርድ በፊት እንደጥፋተኛ ያለመቆጠር መብታቸውን የጣሰ መሆኑን ጠቁሞ ይህ በመሆኑም ከአሁን በኋላ ተከሳሾቹ ለፍርድ ቤት የመከላከያ ምስክሮችን የማቅረብ አቅማቸው አስቸጋሪ እንዳደረገው ጠቅሶአል፡፡ የፌደራል ፖሊስ እና የብሄራዊ ደህንነት እና ጸጥታ ባለስልጣን እንደ ህገመንግስት ...

Read More »

የካናዳ ኩባንያ በደቡብ ኦሞ ነዳጅ ፍለጋ እንዲያካሂድ ተጨማሪ መሬት ተሰጠው

የካቲት ፩፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ካናዲያን ኤክስፕሎረር አፍሪካን ኦይል የተሰኘው ኩባንያ አዲስ መሬት የተሰጠው በምስራቅ የስምጥ ሸለቆ አካባቢ ነው። ኤክስፕሎረር አፍሪካ በደቡብ ኦሞ የነዳጅ ፍለጋ በማካሄድ ላይ ካለው ቱሎው ኦይል ጋር በሸርክና የሚሰራ ድርጅት ነው። ቱሎው ኦይል በደቡብ ኦሞ የሚያካሂደው አሰሳ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ይናገራል። ድርጅቱ ተሳክቶለት ነዳጅ ማውጣት ከጀመረ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው ይሆናል። ምንም እንኳ የኢትዮጵያ ...

Read More »

ፕሬዚዳንት ሞርሲ ምርጫ እንዲደረግ አዘዙ

የካቲት ፩፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የግብጹ ፕሬዚዳንት ሙሀመድ ሞርሲ ጥሪውን ያቀረቡት በአገሪቱ የሚታየው ተቃውሞ እያየለ መምጣቱን ተከትሎ ነው። የአስመራጮች እጥረት በመፈጠሩ ምርጫው ከሚያዚያ እስከ ሰኔ ድረስ ባለው የጊዜ ገደብ እንደሚከናወን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንት ሞርሲና ፓርቲያቸው ምርጫው በየጊዜው የሚካሄደውን የመንገድ ላይ ተቃውሞ ያስቀራል ብለው ያምናሉ። .ግብጽ በሊበራል ዲሞክራሲ አቀንቃኞችና በሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ደጋፊዎች ስትታመስ መቆየቷ ይታወቃል። ፕሬዚዳንት ሞርሲ ...

Read More »

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በኢህአዴግ አመራር ተስፋ መቁረጣቸውን ተናገሩ

የካቲት ፩፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሚያዝያ ወር 2005 የሚካሄደውን የአዲስአበባ እና የአካባቢ ምርጫ ተከትሎ የኢህአዴግ ከፍተኛ ሹማምንት በዘመቻ ከአዲስ አበባ ሕዝብ ጋር በየክፍለ ከተማው በጀመሩት ውይይት ከፍተኛ ትችት እያስተናገዱ መሆኑን በስብሰባዎቹ ላይ የተገኙ ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡ የወደፊቱ የከተማዋ ከንቲባ ይሆናሉ ተብሎ የሚጠበቁትን አቶ ድሪባ ኩማን ጨምሮ የአሁኑ ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ፣ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው፣የመንግስት ተጠሪ ሚ/ር ...

Read More »

የኢህአዴግ አጃቢ ፓርቲዎች ከምርጫው ሊወጡ ይችላሉ ተባለ

የካቲት ፩፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢህአዴግ አጋር እንደሆኑ የሚነገርላቸውና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ እየተባለ በሚጠራው ተሳታፊ የሆኑ ወደ ዘጠኝ የሚጠጉ ፓርቲዎች ለመጪው ምርጫ፤ በምርጫ ቦርድ በኩል የፋይናንስ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት ካለማግኘቱ ጋር ተያይዞ በአጃቢነት ከገቡበት ምርጫ ተገፍተው ሊወጡ እንደሚችሉ ተጠቆመ፡፡ ቀደም ሲል በአቶ ልደቱ አያሌው ይመራ የነበረው ኢዴፓ፣ በአቶ አየለ ጫሚሶ ሊቀመንበርነት የሚመራው ቅንጅት፣መኢብን ፣ራዕይ ...

Read More »

በአዲስ አበባ የሙስሊሞችን ቤት መፈተሽ ቀጥሎአል

የካቲት ፩፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ዘጋቢያችን እንደገለጠው በትናንትናው እለት በፈረንሳይ አካባቢ የሚኖሩ የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት በድንገት ቤታቸው እየተበረበረ ቁራን ፣ የተለያዩ ሲዲዎች እና ሀይማኖታዊ መጽሀፎች ወስደውባቸዋል ። የኢህአዴግ ካድሬዎች እና የደህንነት ሰዎች ናቸው የሙስሊሞችን ቤት እንዲፈተሽ የሚጠቁሙት ያሉን አንድ የአካካቢው ነዋሪ ፣ ፈታሽ ፖሊሶች ምንም አይነት የፍርድ ቤት ትእዛዝ ወረቀት አለመያዛቸውንም ተናግረዋል። የፖሊሶቹ ዋና አላማ ሙስሊሞች በስነልቦና ...

Read More »

አዲሱ የመብራት፣ የውሀና ስልክ ክፍያ ስርአት ችግር እየፈጠረ ነው

የካቲት ፩፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በ ዶ/ር ደብረጺዮን አመራር በቅርቡ ተግባራዊ የተደረገው የመብራት፣ የውሀ እና የስልክ ክፍያዎችን በአንድነት የመክፍል ሂደት በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ መጉላላት እየፈጠረ ነው። ህብረተሰቡ ክፍያዎችን ለመክፈል ረጃጅም ሰልፎችን መሰለፍና በርካታ ሰአታትን መጠበቅ ግዴታው ሆኗል ስራውን እንዲተገብሩ የተመረጡት በሙሉ ኢህአዴግ ካድሬዎች ሲሆኑ ፣ የኢህአዴግ አባላት ያልሆኑ የየድርጅቶቹ የቀድሞ ሰራተኞች ተንሳፋፊዎች ሆነዋል። መንግስት የህብረተሰቡን እንግልት ይቀንሳል ...

Read More »