የደብረማርቆስ የመሰናዶ ተማሪዎች የመንግስትን ፖሊሲ ተቃወሙ

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ተማሪዎች ኢህአዴግን እንዲመርጡ በሚል በግዳጅ በተዘጋጀው የፖለቲካ ስልጠና ላይ ተማሪዎች ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን ሰጥተዋል ። ኢህአዴግ እነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን የመሰሉ ሰዎችን አሸባሪዎች ማለቱ ትክክል አለመሆኑን የሚገልጹት ተማሪዎች፣ ኢህአዴግን የሚበልጡት በመሉ  አሸባሪ እያለ እንደሚፈርጃቸው ተናግረዋል ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የሚኖርበት ቤት 400 ሺ ብር እንደሚከፈልበት የተናገሩት ተማሪዎች፣ አባይን መገደብ ያልቻለ መንግስት እንዴት ...

Read More »

በአዳማ በሚካሄደው ስብሰባ የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሳይቀሩ ሞባይል ስልክ ይዘው እንዳይገቡ ተከለከሉ

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ከመላው አገሪቱ ለተውጣጡ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች መጪውን ምርጫ በተመለከተ ስልጠና እየሰጠ ሲሆን፣ ከስልጠናው በፊት ማንኛውም ባለስልጣን ስልክ ይዞ መግባት እንደማይችል ጥብቅ የሆነ መልእክት በመተላለፉ፣ ሁሉም ባለስልጣናት ስልካቸውን መኪናቸው ውስጥ እየተዉ ወይም ለሹፌሮቻቸው እየሰጡ መግባታቸው ታውቋል። ወደ ስብሰባው የሚገባ ሰው ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን መያዙንና አለመያዙን ለማረጋገጥ  ጥብቅ ፍተሻ እንደሚካሄድበት የክልሉ ዘጋቢያችን ...

Read More »

እነ አቶ አንጋው ተገኝ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ጥቅምት ወር በጎንደር፣ በትግራይና በጎጃም አካባቢዎች የተያዙ የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች ፍድር ቤት ቀርበው የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል። ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው የሰማያዊ፣ የአንድነትና የመኢአድ ፓርቲዎች የዞን አመራሮች  ታህሳስ 21 ቀን 2007 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ፣ አመራሮቹ ለ3ኛ ጊዜ የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡ “ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም፣ የምስክር ቃል አልሰማሁም፣ ግብረ-አበሮችን አልያዝኩም ...

Read More »

የኦሮምያ ክልል የአድማ ብተና ዋና አዛዥ እስከ ጠባቂዎቻቸው አረፉ

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል  በተለይም በአምቦ፣ በአለማያና በሌሎችም ዩኒቨርስቲዎች ለተፈጸሙ ግድያዎችና  በሌሎች  አካባቢዎች ለደረሱ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተጠያቂ የሆኑት ኮማንደር ፣ ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓም ሲያሽከረክሩት የነበረው መኪና ተገልብጦ ከ3 ጠባቂዎቻቸው ጋር በሂርናና አሰበ ተፈሪ መካከል በሚገኝ አንድ ገደላማ ቦታ ላይ ገብተው ህይወታቸው ወዲያውኑ አልፎአል። ኮማንደሩ የተሳፈሩበት ዘመናዊ ላንድ ክሩዘር  ወደ ኢትዮጵያ ...

Read More »

በኮምቦልቻ የገዢውን ፓርቲ ካድሬዎች በጥያቄ ያፋጣጡ ተማሪዎች ህዝብ ልታሳምጹ ነው የሚል ማስጠንቀቂያዎች ደረሳቸው

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው እሮብ ጀምሮ ለ3 ቀናት በተካሄደው የመሰናዶና የመምህራን የፖለቲካ ስልጠና ላይ የገዚውን ፓርቲ ካድሬዎች በጥያቄ ከማፋጠጥ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ በሚታየው ዘረኝነት፣ የፍትህ እጦትና ሙስና ላይ አስተያየቶችን የሰጡ ተማሪዎች ከስብሰባው መጠናቀቅ በሁዋላ ተማሪውንና ህዝቡን ለአመጽ ለማነሳሳት አስባችሁዋል በሚል ማስጠንቀቂያና ባስፈራሪያ እንደደረሳቸው ዘጋቢያችን ገልጻለች። ለተማሪዎች በሚሊኒየም ትምህርት ቤት በፕላዝማ የተደገፈ የ3 ቀናት ስልጠና ሲሰጥ፣ ለመምህራን ...

Read More »

ኢትዮጵያ ለወሲብ ንግድና ለህገወጥ የሰዎች ዝውውር መነሻ አገር ሆናለች ሲል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት ባወጣው የ2014 ሪፖርት ኢትዮጵያ ለግዳጅ ሥራ፣  ለወሲብ ንግድና  ለሕገወጥ የሰዎች ዝውውር የተዳረጉ ወንዶች፣ ሴቶች እና ሕፃናት መነሻ፤ በተወሰነ ደረጃም መዳረሻ አገር ናት ብሎአል። አዲስ አበባ የሚገኘው ዋና የገበያ ማዕከል ከአፍሪካ ቀዳሚው የወሲብ ንግድ ቤቶች መገኛ ነው የሚለው ሪፖርቱ፣  ዕድሜያቸው እስከ 8 ዓመት የሚሆኑ ልጃገረዶች በነዚህ ቤቶች በሴተኛ አዳሪነት ተሰማርተዋል ይላል። ...

Read More »

የኢንተርኔት እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መረጃዎች ላይ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር የሚያደርግ አዋጅ ተረቀቀ

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን  ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡ የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት ሚዲያውን የሚመለከት ነው፡፡ በዚህ አዋጅ ...

Read More »

ከድንበር ጋር በተያያዘ በአማራና በትግራይ ክልል ከፍተኛ ውጥረት ነግሶአል

ታኀሳስ ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት ታህሳስ 16 ቀን 2007 ዓም በሶረቃ ከተማ ከ70 ያላነሱ ከትግራይ ክልል የመጡ ታጣቂዎች፣ ከምስላል ወደ  ስላንዴ በረሃ የሚሰራውን መንገድ ለማስቆም ተኩስ በመክፈታቸው 2 አርሶ አደሮች ሲቆስሉ፣ በአብራጅራ ወረዳ የሚገኙ  ጸረ ሽምቅ እየተባሉ የሚጠሩ ሃይሎች ከህዝቡ ጋር በመሆን   የአጸፋ ተኩስ በመክፈታቸው ታጣቂዎች ከአካባቢው ተሰውረዋል። ፌደራል ፖሊስ ወደ አካባቢው በመሄድ ህዝቡን ...

Read More »

ሄሊኮፕተር ጠልፈው የተሰወሩት በመልካም ሁኔታ ላይ ናቸው ተባለ

ታኀሳስ ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአየር ሃይል ባልደረባ የሆኑት ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ ከበረራ ቴክኒሻኑ ጸጋ ብርሃን ግደይ ጋር በጋራ በመሆን የሚያበሩትን ሄሊኮፕተር ይዘው ከጠፉ በሁዋላ በአሁኑ ጊዜ በምልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የኢሳት ምንጮች ግልጸዋል። ምንጮቹ አብራሪዎቹ ያሉበትን ቦታ ለመግለጽ ፈቃደኛ ባይሆኑም፣ በአሁኑ ጊዜ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል። ኢሳት ...

Read More »

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በ15 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎችን ሊያደርግ ነው

ታኀሳስ ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ያወጣውን ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩን ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓ.ም ይፋ ሲያደርግ፣ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩም ለ2 ወራት የሚቆይ እንደሚሆን አስታውቋል። የትብብሩ አመራሮች በሰማያዊ ጽ/ቤት የሰጡትን  መግለጫ ተንተርሶ ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው በሁለተኛ ዙር የትብብሩ መርሃ ግብር መሰረት የካቲት 15 ቀን 2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት ...

Read More »