የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበርን ለማካለል የተጀመረ ስራ እንደሌለ የኮምኒኬሽንና ሚዲያ ባለሙያዎች ደጋግመው እንዲሰሩ የአቶ ጌታቸው ረዳ ጽ/ቤት አሳሰበ፡፡

ታኀሳስ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመንግስት ኮምንኬሽን ጽ/ቤት ለኮምኒኬሽን ባለሙያዎችና ለጋዜጠኞች ባሰራጨው የመንግስት የሳምንቱ አቋም መግለጫ በኢትዮ ሱዳን ድንበር ጉዳይ የተጀመረ ስራ እንደሌለ እንዲናገሩ አቅጣጫ አስቀምጧል። “መንግስት ሁሉም የኢትዮጵያ ድንበሮችን የማካለል ስራ ጠቃሚ መሆኑን ይረዳል”ያለው ፣ የአቋም መግለጫው፣ ሆኖም የኢትዮ-ሱዳንን ድንበር ለማካለል አሁን ምንም የተደረገ ስምምነት የለም።» በማለት በሱዳን ሚዲያዎች በተደጋጋሚ እየተዘገበ ያለውን ጉዳይ ለማስተባበል ...

Read More »

የካራቶሪው ባለቤት መሬቴን ትነኩና የህንድን ሃያልነት ታያላችሁ ሲሉ የመንግስት ባለስልጣናትን አስጠነቀቁ

ታኀሳስ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በጋምቤላ 300 ሺ ሄክታር መሬት ተሰጥቷቸው ለማልማት ባለመቻላቸው ከፍተኛ ትችት የሚቀርብባቸው የካሩቱሪ አግሮ ፕሮዳክትስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ መሥራችና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሳይ ራማክሪሽና ከሪፖርትር ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፣ የጋምቤላ ክልል መንግስት በግድ ሳይፈልጉ በፈለጉት ዋጋ ከፍለው 300 ሺ ሄክታር መሬት እንደሰጧቸው ተናግረዋል። እኔ የጠየቁት 10 ሺ ሄክታር ብቻ ነው ያሉት ባለሃብቱ፣ ...

Read More »

ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ሲፒጄ በኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን ማሰር መቀጠሉ እያሳሰበው እንደመጣ አሳወቀ።

ታኀሳስ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የነገረ ኢትዮጵያ ዘጋቢ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እለተ ዐርብ በጸጥታ ኃይሎች ከመንገድ ላይ ተይዞ የታሰረ ሲሆን፣የኦሮሚያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ጋዜጠኛ ፍቃዱ ሚርካናም በደኅንነት ኃይሎች ተይዞ ያለበት ቦታ እንደማይታወቅ ጂፒጄ አስታውቋል። በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔት እየከፋ መምጣቱንና በአፍሪካ ውስጥ ካሉ አገራት ጋዜጠኞችን በማሰር የኢትዮጵያ መንግስት ከቀዳሚዎቹ ተርታ መቀመጡን ሲፒጄ በሪፖርቱ አስታውቋል። ...

Read More »

በኮርያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

ታኀሳስ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያውያኑ ለሱዳን የሚሰጠውን መሬት በመቃወምና እንዲሁም በኦሮምያ የደረሰውን ጭፈጨፋ በማውገዝ በኮርያ ሲዖል ከተማ በሱዳን እና በኢትዮጵያ ኢምባሲዎች ፈት ለፊት የታቃዉሞ ሰልፍ አድርገዋል። ኢትዮጵያውያኑ ወደ ሱዳን ኢምባሲ በማምራት የኢትዮጵያ መንግስት አሳልፎ ለመስጠት ያሰበዉ መሬት የኢትዮጵያ ሕዝብ እየተቃወሙ በመሆኑ የሱዳን መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር ለወደፊቱ ለሚፈጠረው ዘላቂ ሰላም እና ጥሩ ጉርብትና ሲል ከመንግስት ...

Read More »

አቶ በቀለ ገርባና ሌሎች የኦፌኮ መሪዎች ታሰሩ

ኢሳት (ታህሳስ 14 ፣ 2008) የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ኦፌኮ ከፍተኛ አመራር አቶ በቀለ ገርባ ከሰዓታት በፊት በመንግስት ሃይሎች ታሰሩ። 21 ደህንነቶችና ታጣቂዎች አዳማ የሚገኘውን የአቶ በቀለ ገርባ መኖሪያ ቤት ለ 5 ሰዓታት ያህል ሲበረብሩና ሲፈትሹ እንደዋሉ ለማወቅ ተችሏል። ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ ለአምስት ሰዓታት ከተካሄደው ፍተሻና ብርበራ በኋላ፣ 12 ሰዓት ላይ አቶ በቀለ ገርባ በመኪና ወደአዲስ አበባ ተወስደዋል ተብሏል። የኦፌኮ ...

Read More »

መንግስት ታዋቂ የተቃዋሚ ድርጅት መሪዎችን እየያዘ በማስር ላይ ነው

ታኀሳስ ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ መንግስት ወጣቶችን በየአካባቢው እያፈሰ ከማሰሩም በላይ የተቃዋሚ መሪዎችን ሲያስፈራራ ከቆየ በሁዋላ መሪዎችን ይዞ ማሰር ጀምሯል። በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ም/ል ሊ/መንበር አቶ በቀለ ገርባ እንዲሁም የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ዋና ጸሃፊ የሆኑት የህግ ባለሙያውና ከ10 አመት በፊት በተደረገው ምርጫ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ ...

Read More »

ኢሳት ስርጭቱን ለማስጀመር በሂደት ላይ መሆኑን የስራ አመራር ክፍል አስታወቀ

ታኀሳስ ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ገንዘብ በማፍሰስና በዲፐሎማሲ ዘመቻ የኢሳትን የሳተላይት ስርጭት ለማፈን ተደጋጋሚ ጥረት ሲያደርግ ከቆየ በሁዋላ፣ በኦሮምያ የተነሳውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ ስርጭቱ እንደገና ለቀናት እንዲቋረጥ አድርጓል። ስርጭቱ መቋረጡን ተከትሎ ከኢትዮጵያ ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን የደረሱን ሲሆን፣ ኢሳት ወደ አየር ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ስራ አመራር ክፍል ገልጿል። ኢሳት በጥቂት ቀናት ውስጥ ...

Read More »

የዞን 9 ጦማሪያን በአቃቤሕግ ይግባኝ ተጠየቀባቸው

ታኀሳስ ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በነሶልያና መዝገብ ከሽብር ነፃ የተባሉት አምስት ተከሳሾች ላይ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ያቀረበው ይግባኝ ያስቀርባል በሚል ለታኅሣሥ 20 ቀን 2008 እንዲቀርቡ ተብለዋል። መጥሪያው የደረሰው የበፍቃዱ ኃይሉ ሰነድ እንደሚያሳየው ይግባኝ የተባለባቸው በሌለችበት የተከሰሰችው ሶልያና ሽመልስ እና በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አጥናፉ ብርሀኔ እንዲሁም አቤል ዋበላ ናቸው። በፍቃዱ ኃይሉ የተቀየረለትን ‘አመጽ ...

Read More »

ታንዛኒያ በሕገ-ወጥ ስደተኞች መጨናነቋን አሳወቀች

ታኀሳስ ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድና ቪዛ ሳይዙ ድንበር ተሻግረው ወደ ታንዛኒያ የሚገቡ የምስራቅ አፍሪካ ስደተኞች ቁጥር እያደር መጨሩንና ሁኔታው ከአገሪቱ አቅም በላይ መሆኑን የታንዛኒያው የአገር ውስጥ ሚንስቴር ቻርለስ ኪታዋንጋ አስታወቁ። አብዛሃኞቹ ስደተኞች የምስራቅ አፍሪካ ዜጎች ሲሆኑ የኢትዮጵያ፣ሶማሊያና ኤርትራ ዜጎች ቅድሚያውን ይወስዳሉ። በቅርቡ 42 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ዳሬሰላም ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ሲገቡ መያዛቸውን ተከትሎ ሚኒስቴሩ ...

Read More »

የማዳበሪያ እዳ እና ረሃብ በመሸሽ አርሶ አደሮች ወደ አዲስ አበባ እየተሰደዱ ነው

ታኀሳስ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሃብ በመሸሽ እንዲሁም የመንግስትን የማዳበሪያ እዳ ለመክፈል ሲሉ በርካታ አርሶደሮች ወደ አዲስ አበባ እየተሰደዱ ሲሆን፣ አርሶ አደሮቹ በተለይም ዘነበወርቅ በሚባለው ቦታ ሰፍረው እንደሚገኙ ታውቋል። የ7 ልጆች አባት የሆኑት አርሶአደር ከጎጃም ተሰደው መምጣታቸውን ይናገራሉ። መነኩሴ እናታቸው ይዘው መምጣታቸውን የሚገልጹት አርሶ አደሩ በረሃቡና በማዳበሪያ እዳ ምክንያት እርሳቸው እና ሌሎች በርካታ አርሶአደሮች ...

Read More »