በማስተር ፕላን ተቃውሞ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ140 ማለፉን መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ

ኢሳት (ታህሳስ 29 ፥ 2008) በተለያዩ የኦሮሚያ የክልል ከተሞች ቀጥሎ የሚገኘው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተቃውሞ በመንግስት ወታደሮች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር በትንሹ 140 መድረሱንና ተቃውሞው አለመርገቡን በርካታ አለም-አቀፍ መገናኛ ብዙሃን አርብ ዘገቡ። ዳግም አገርሽቶ የሚገኘው ይኸው ተቃውሞ አርብ በምዕራብ ሃረርጌ በሚገኙ ሂርናና ጭሮ (አሰበ ተፈሪ) ከተማ መቀስቀሱንና፣ የመንግስት ወታደሮችና ፖሊሶች እርምጃ መውሰዳቸውን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል። ሁለተኛ ወሩን በያዘውና ...

Read More »

በአርባምንጭ የሚገኘው የአሜሪካ ሰው አልባ አውሮፕላን ጣቢያ በኢትዮጵያ ጥያቄ የተዘጋ መሆኑ ታወቀ

ኢሳት (ታህሳስ 29 2008) በደቡብ ኢትዮጵያ አርባ ምንጭ ከተማ ላለፉት 5 አመታት ያህል ሲያገለግል የቆየው የአሜሪካ የሰው አልባ የስለላና የውጊያ አውሮፕላን (ድሮን) ጣቢያ መዘጋት የሃገሪቱን ግንኙነት የሚጎዳ ዕርምጃ መሆኑ ተመልክቷል። ዩ ኤስ አሜሪካ የድሮን ጣቢያው አላስፈላጊ በመሆኑ መዘጋቱን በወቅቱ ብትገልጽም፣ የኢትዮጵያ መንግስት ቃለ አቀባይ ረቡዕ በሰጡት መግለጫ የድሮን ጣቢያው በኢትዮጵያ ጥያቄ መዘጋቱን ይፋ አድርገዋል። በዓለም-አቀፍ ደረጃ በውጭ ግንኙነት ፖሊሲዎች ላይ ...

Read More »

አቶ በቀለ ነገአ በቁም እስር ላይ ናቸው

ታኀሳስ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦፌዴን ሊቀመንበር አቶ በቀለ ነገአ በደህንነት ሃይሎች ታፍነው ተወስደው ድብደባ ከተፈጸመባቸው በሁዋላ፣ ከቤት ወጥተው ስራቸውን ለማከናወን ባለመቻላቸው በቁም እስር ላይ እንደሚገኙ ከባልደረቦቻቸው የተገኘው መረጃ አመልክቷል። ሌላው የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ ባልታወቀ ስፍራ ተወስደው የታሰሩ ሲሆን፣ አቶ በቀለ ነገአ ግን ማንኛውንም አይነት መግለጫ ለመገናኛ ብዙሃን እንዳይሰጡ እንዲሁም ከቤታቸው እንዳይወጡ ...

Read More »

በዘላለም ወርቃገኘሁ መዝገብ የተከሰሱት ታዋቂ ፖለቲከኞች በድጋሜ ተቀጠሩ

ታኀሳስ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሽብረተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው ከፍተኛው ፍርድ ቤት በነጻ ያሰናበታቸው ታዋቂዎቹ ፖለቲከኞች ሃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም አብርሃም ሰለሞን ፣ አቃቢ ህግ ይግባኝ ጠይቆባቸው ነጻ ከተባሉትበት ከነሃሴ 14 ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛሉ። ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው ታህሳስ 29/2008 ዓ.ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኑ ላይ ብይን ይሰጣል ተብሎ ...

Read More »

በኢትዮጵያ የአእምሮ በሽተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው

ታኀሳስ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከቅርብ ኣመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የአእምሮ ጤና መቃወስን ጨምሮ ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፉ መምጣታቸውን፣ መንግስትም ችግሩን ለመከላከል በቂ የሆነ ጥረት እንዳላደረገ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ አመለከተ፡፡ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች መካከል የካንሰር ሕመም ፣ የአእምሮ ህመም፣ ከውፍረት ጋር የተያያዙ የጤና ችግሮች፣ ከአልኮልና የትምባሆ እንዲሁም ከአደገኛ ዕጾች ጋር የተያያዙ የጤና ...

Read More »

ኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች ያነሱት የመብት ጥያቄ ተገቢ ነው፣ የትጥቅ ትግል የጀመሩትን መደገፍ አለብን ሲሉ ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ አስታወቁ

ኢሳት (ታህሳስ 29 ፣ 2008) የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች ያነሱት የመብት ጥያቄ ተገቢና የሚግደገፍ ነው ሲሉ ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ምሁር ገለጹ። በከተሞች መስፋት ሃብታም የመሆን እድል የልተመቻቸለት አርሶ አደሮች ወደ ድህነት እየተገፉ፣ ባለጊዜ በዕርሱ መሬት እንዲበለጽግ መንገድ ሲጠርግ ተቃውሞ መጀመራቸው ትክክል ነው ያሉት ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ፣ ይህ በኦሮሞዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ላይ ሊደርስ የሚችል በመሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሊያወግዙት እንደሚገባ ለኢሳት በሰጡት ...

Read More »

የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተከትሎ የተነሳው ህዝባዊ አመጽ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ኢሳት (ታህሳስ 29, 2008) የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተከትሎ የተነሳው ህዝባዊ አመጽ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በኦሮሚያ ክልል የተጀመረው ተቃውሞ ትናንትም በተለያዩ አካባቢዎች ቀጥሎ መዋሉ ታወቀ። በትናንትናው ዕለትም በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች እና በአንዳንድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መንግስት እየወሰደ ያለውን ዕርምጃ በመቃወም የተለያዩ ህዝባዊ እምቢተኝነቶች መካሄዳቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በትናንትናው ዕለት የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ 5 ኪሎ ካምፓስ ተማሪዎች ለገና በዓል የተዘጋጀውን ምግብ ባለመመገብ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ አቡነ መሮቆርዮስ ኢትዮጵያውያና በፍቅርና በሰላም ተከባብረው እንዲኖሩ፣ አገራቸውን እንዲጠብቁ ጥሪ አቀረቡ

ኢሳት (ታህሳስ 29 ፡ 2008) ኢትዮጵያውያን በፍቅርና በሰላም ተከባብረው እንዲኖሩ፣ አድነታቸውን እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ አቡነ መሮቆርዮስ ጥሪ አቀረቡ፥ በኦሮሚያ ክልል ለተቃውሞ አደባባይ በወጡ ኢትዮጵያውያን ላይ መንግስት በወሰደው የመግደልና የእስር እርምጃ ማዘናቸውን ገልጸው፣ ለሟች ለቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል። ፓትሪያርኩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ የኢየሱስ ክርስቶስን 2ሺ 8ኛ አመት የልደት በዓል በማስመልከት ለኢትዮጵያውያን ትናንት ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ግዛት ወደሱዳን ተላልፎ ...

Read More »

በኦሮምያ የሚካሄደውን ተቃውሞ ተከትሎ የታሰሩት እንደፈቱ ሂውማን ራይትስ ወች ጠየቀ

ታኀሳስ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሰብአዊ መብት ድርጅቱ በምስራቅ አፍሪካ ተመራማሪው ፌሊክ ሆርን በኩል ባወጣው መግለጫ፣ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ መታሰራቸውን ተከትሎ ግጭቱ እየተባባሰ መምጣቱንና በእስካሁኑ ተቃውሞ 140 ሰዎች መገደላቸውን ጠቅሷል። አቶ በቀለ ገርባና ሌሎችም እስረኞች እንዲፈቱ የጠየቀው ሂውማን ራይትስ ወች፣ ዜጎች ሃሳባቸውን በነጻነት እንዲገልጹ እንዲፈቀድላቸው፣ አርሶአደሮችን በዘፈቀደ ማፈናቀል እንዲቆምና በቂ ምክክር እንዲደረግ አሳስቧል። ...

Read More »

ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት መከሰቱን ነጋዴዎች ተናገሩ

ታኀሳስ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የንግድ ድርጅት ባለቤቶች ለኢሳት እንደገለጹት በአሁኑ ሰአት የተከሰተው የዶላር እጥረት ከምርጫ 97 በሁዋላ ከፍተኛው ነው። በአስመጭነትና ላኪነት ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በውጭ ምንዛሬ እጥረት ስራቸውን ለመስራት በማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። ፋብሪካዎች የመለዋወጫ እቃዎችን ለመግዛት በመቸገራቸው እንቅስቃሴያቸው በእጅጉ ተዳክሟል። በተለይ የግንባታ እንቅስቃሴው በእጅጉ መዳከሙን ነጋዴዎች ይገልጻሉ። በአገሪቱ የተፈጠረውን ከፍተኛ ድርቅ ለማቋቋም መንግስት ...

Read More »