Amsterdam

10 ሺ የሚጠጉ የሞያሌ ከተማ ተፈናቃዮች ስደት መጠየቃቸውን ተመድ አስታወቀ

10 ሺ የሚጠጉ የሞያሌ ከተማ ተፈናቃዮች ስደት መጠየቃቸውን ተመድ አስታወቀ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 10 ቀን 2010 ዓ/ም) ኬንያ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽነር ባወጣው ዘገባ፣ እስካሁን 9 ሺ 700 ስደተኞች ከኦሮም ክልል ሞያሌ ከተማ ተፈናቅለው ኬንያ ገብተዋል። ስደተኞቹ 13 ሰዎች በወታደሮች መገደላቸውን እንደተናገሩ ተመድ አስታውቛል። በላይነሽ ታደሰ የተባሉ የ2 ልጆች እናት ፣ ጎረቤታቸው ከትምህርት ቤት የወላጆች ስብሰባ ሲመለስ በጥይት ...

Read More »

መንግስት የአገሪቱን ችግር በሃይል ለመፍታት በመሞከሩ በህዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ ነው ሲል ኦፌኮ ገለጸ

መንግስት የአገሪቱን ችግር በሃይል ለመፍታት በመሞከሩ በህዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ ነው ሲል ኦፌኮ ገለጸ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 10 ቀን 2010 ዓ/ም) የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ባወጣው መግለጫ፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያገራችንን ችግር እያባበሰ ስለሆነ መንግስት አዋጁን አንስቶ ከሃቀኛ ተቃዋሚዎች ጋር ድርድር እንዲያካሂድና ብሄራዊ መግባባት እንዲፈጠር አሳስቧል። ከዚህ በፊት በአገሪቱ ታይቶ በማይታወቅ ዓይነት ከ700 ሺ በላይ የኦሮሞ ህዝብ በኢትዮጵያ ውስጥ ተዘዋውሮ ...

Read More »

ኤርትራ በኢህአዴግ የቀረበባትን ክስ አጣጣለች

ኤርትራ በኢህአዴግ የቀረበባትን ክስ አጣጣለች (ኢሳት ዜና ማጋቢት 10 ቀን 2010 ዓ/ም) ኤርትራ ኢትዮጵያ እንዳትረጋጋ እያደረገች ነው በማለት በህወሃት ኢህአዴግ አገዛዝ በኩል የቀረበውን ክስ፣ ኤርትራ አጣጥላዋለች። “ኢትዮጵያ ችግሩን ውጫዊ ለማድረግ ከመፈልግ ይልቅ፣ እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ተቃውሞውና አለመረጋጋት ለመፍታት ብትሰራ ይሻላታል” ስትል ገልጻለች። የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ ገብረ መስቀል ለብሉምበርግ እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለውስጣዊ ችግሩ ውጫዊ ምክንያት እየፈለገ፣ የህዝቡን የትኩረት አቅጣጫ ...

Read More »

በአፍሪካ ኮንፌድሬሽን ዋንጫ የኢትዮጵያው ወላይታ ዲቻ ከግምት ውጪ የግብጹን ዛማሊክ አሸንፎ ወደ ቀጣዩ ዙር አላፊ ቡድን ሆነ

በአፍሪካ ኮንፌድሬሽን ዋንጫ የኢትዮጵያው ወላይታ ዲቻ ከግምት ውጪ የግብጹን ዛማሊክ አሸንፎ ወደ ቀጣዩ ዙር አላፊ ቡድን ሆነ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 10 ቀን 2010 ዓ/ም) የግብጹ አንጋፋ ቡድን ዛማሌክና የኢትዮጵያው ወላይታ ዲቻ በመዲናዋ ካይሮ 2 ሽህ ተመልካቾች በተገኙበት አል-ሰላም መጫወቻ ሜዳ ባደረጉት ጫወታ በመደበኛ የጫወታ ክፍለ ጊዜ ዛማሌክ 2-1 ቢያሸንፍም በተመሳሳይ ውጤት ወላይታ ዲቻ 2-1 በማሸነፉ 3-3 አቻ ሆኑ። አሸናፊውን ቡድን ...

Read More »

በሞያሌ ወታደሮችን የጫኑ ሁለት ኦራል መኪኖች በታጣቂዎች ተመተው ከተገለበጡ በሁዋላ በርካታ ወታደሮች አለቁ

በሞያሌ ወታደሮችን የጫኑ ሁለት ኦራል መኪኖች በታጣቂዎች ተመተው ከተገለበጡ በሁዋላ በርካታ ወታደሮች አለቁ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 07 ቀን 2010 ዓ/ም) ኦነግ የሞቱት ወታደሮች ቁጥር 72 ነው ይላል። የአካባቢው ነዋሪዎች ደግሞ የሟቾች ቁጥር 50 አካባቢ ነው ይላሉ። ጥቃቱን ተከትሎም ኬንያ ድንበሯን ዘግታለች። የኢሳት የአካባቢው ምንጮች እንደገለጹት 147 እና ወጀሌ በሚባለው አካባቢ አንድ ሙሉ ወታደሮችን የጫነ ኦራል መኪና በኦነግ ታጣቂዎች እንደተመታ ከሶስት ...

Read More »

የሁመራ ወረዳ አስተዳደር የፌደራል መንግስት ተወካዮች በአማርኛ እንዳይናገሩ ከለከለ

የሁመራ ወረዳ አስተዳደር የፌደራል መንግስት ተወካዮች በአማርኛ እንዳይናገሩ ከለከለ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 07 ቀን 2010 ዓ/ም) የሁመራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢሳያስ ከፌደራል መንግስት ተወክለው ባለሃብቶችን በብድር ጉዳይ ለማወያየት የሄዱ ባለስልጣናት በአማርኛ ስብሰባ እንዳይመሩ ከልክለዋል። መጋቢት 5 /2010 ዓ.ም በሁመራ ከተማ አስተዳደር አዳራሽ ከፌደራል መንግስቱ የተወከሉ አቶ አማኑኤል ተስፉ የተባሉ ግለሰብ ስብሰባውን በአማርኛ ሲመሩ የወረዳው አስተዳደሪ “በአማርኛ ስብሰባ ማድረግ አይቻልም። ስብሰባው ...

Read More »

ከ51 በመቶ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ወጣት በአደንዛዥ እጽ ተጠቅቷል ተባለ

ከ51 በመቶ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ወጣት በአደንዛዥ እጽ ተጠቅቷል ተባለ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 07 ቀን 2010 ዓ/ም) ዲኬቲ ኢትዮጵያ ባዘጋጀው የወጣቶችና የስነ ተዋልዶ የምክክር ዝግጅት ላይ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ አብዛሃኞቹ ወጣቶች በአደንዛዥ ሱሶች ተጠቂ መሆናቸውንና ራስን የማጥፋት እርምጃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ መምጣቱ ተገልጿል። በኢትዮጵያ እድሜያቸው ከ10 እስከ 24 ዓመት ከሚሆናቸው ወጣቶች ውስጥ 51 ከመቶ ያህሉ ጫት ቃሚዎች፣ 45.6 ከመቶ የሚሆኑት ...

Read More »

ሼክ ሙሃመድ ሁሴን አላሙዲን የታሰሩበት ቦታ እንደማይታወቅ ተገለጸ

ሼክ ሙሃመድ ሁሴን አላሙዲን የታሰሩበት ቦታ እንደማይታወቅ ተገለጸ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 07 ቀን 2010 ዓ/ም) ዘ ኒውዮርክ ታይምስ ይዞት በወጣው ሰፊ ዘገባ ከአላሙዲን ጋር አብረው ታስረው ልኡላንና ባለሀብቶች ከእስር ሲፈቱ አላሙዲን ግን እስካሁን አልተፈቱም። የአላሙዲን የፕሬስ ክፍል ፣ ባለሃብቱ ሪትዝ ካርልቶን በሚባለው ሆቴል ታስረው ከቆዩ በሁዋላ ወደ ሌላ ሆቴል መዘዋወራቸውን ቤተሰቦቹ ቢናገሩም፣ የታሰሩበትን ቦታ እንደማያውቁ አስታውቋል። ከቤተሰቦቻቸው ጋር በየጊዜው እንደሚገናኙና ...

Read More »

ጠንካራ መግለጫ በመስጠት የሚታወቁት አቶ ታዬ ደንደዓ ታሰሩ

ጠንካራ መግለጫ በመስጠት የሚታወቁት አቶ ታዬ ደንደዓ ታሰሩ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 06 ቀን 2010 ዓ/ም) በሞያሌ የደረሰውን ጭፍጨፋ ሆን ተብሎ የታቀደ እንጅ በስህተት የተፈጸመ ነው ብለው ለማመን እንደሚቸገሩ የገለጹት የኦሮምያ ፍትህ ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ታዬ ደንደዓ በወታደራዊ እዙ ትዕዛዝ እንዲታሰሩ ተደርጓል። አቶ ታዬ ለአሜሪካ እና ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ መግለጫዎችን ከሰጡ በሁዋላ ብዙዎች እንደሚታሰሩ ግምታቸውን ሰጥተው ነበር። አቶ ታዬ ...

Read More »

የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት ይቃወሙኛል የሚላቸውን የዲያስፖራ ቤተሰቦች ማሰሩን ቀጥሎአል

የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት ይቃወሙኛል የሚላቸውን የዲያስፖራ ቤተሰቦች ማሰሩን ቀጥሎአል (ኢሳት ዜና ማጋቢት 06 ቀን 2010 ዓ/ም) የሶማሊ ክልልን ህዝብ እንደ ግል ንብረቱ አይቶ ያሻውን እርምጃ ያለ ከልካይ እየወሰደ እንደሆነ የሚነገርለት የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ ኢሌ ፣ አሁንም ይቃወሙኛል የሚላቸውን የዲያስፖራ አባላት ቤተሰቦችን ማሰሩን መቀጠሉን ምንጮች ገልጸዋል። እንግሊዝ አገር የሚኖረውና የአብዲ ኢሌን አገዛዝ በመቃወም ትችት የሚያቀርበው አብዲራሽድ አሊ ሹዋ ዘመዶች ...

Read More »