.የኢሳት አማርኛ ዜና

ባለፉት 10 አመታት በአዲስ አበባ የተገነባው ከአጼ ሚኒሊክ ጀምሮ ከተገነባው ይበልጣል ሲሉ አቶ ኩማ ደመቅሳ ተናገሩ

ህዳር ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከንቲባው ይህን የተናገሩት  በቅርቡ የአዲስ አበባ 125ኛ አመት ክብረ በአል ሲጠናቀቅ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ነው። አቶ ኩማ ከተማዋን የቆረቆሩትን እና በከተማዋ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉትን በሙሉ በማውገዝ የኢህአዴግን ስራ ለማሞካሸት ሞክረዋል። በነገሥታቱ ዘመን የከተማዋ የመሬት ይዞታ ለመኳንንት፣ ለመሳፍንትና ለጦር አበጋዞች ተከፋፍሎ አብዛኛው የከተማዋ ነዋሪዎች ሲሰቃዩ እንደኖሩ፣ የከተማዋ ዕድገት ማስተር ፕላንን ያልተከተለ በመሆኑና በመኳንንቱና ...

Read More »

በኢትዮጵያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ጎዳና ተዳዳሪዎች አሉ

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ ከተማ ከአንድ መቶ ሺህ በላይ ጎዳና ተዳዳሪዎች መኖራቸውን የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ጥናት አመለከተ። የኢትዮጵያ መንግስት ማእከላዊ ስታትስቲክ መስሪያ ቤት ደግሞ በአዲስ አበባ ያሉት ጎዳና ተዳዳሪዎች 60 000 ብቻ ናቸው የሚል መረጃ አሰራጭቷል። የተባበሩት መንግስታት የአለም አቀፉ የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ እንዳመለከተው በኢትዩኦጵያ በአጠቃላይ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ጎዳና ተዳዳሪዎች ...

Read More »

በአዲስ አበባ በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ፈርሰዋል

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአዲስ አበባ መስተዳድር በአዲስ አበባ ከተማ በሁለት ክፍለ ከተሞች ብቻ ያፈረሳቸው ቤቶች በሺዎች የሚቆጠሩ መሆናቸውን አዲስ አበባ ከተማ የሚታተመው አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ዘገበ ። ሳምንታዊው የእንግሊዘኛ ጋዜጣ አዲስ ፎርቹን እሁድ ዕለት እንደዘገበው በቦሌ ክፍለከተማና በንፋስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተሞች የፈረሱ ቤቶች 7ሺህ ደርሰዋል። መስተዳድሩ ከገበሬዎች በግዢ ወደ ነዋሪዎች የተላለፉት መሬቶች ሕጋዊ ማረጋገጫ የላቸውም ...

Read More »

839 ሺህ 580 ኢትዮጵያውያን የፌስቡክ ተጠቃሚ ናቸው

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከዓለማችን በሕዝብ ቁጥር ከቀደሚዎቹ 15 ሐገራት ውስጥ የምትገኘው ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ በ88ኛ ደረጃ ላይ መገኘትዋን አንድ ጥናት አረጋገጠ ። ሶሻል ቤከርስ የተባለ ተቐም ይፋ ባደረገው መረጃ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ ከማህበራዊ መገናኛ ማለትም ፌስ ቡክ የሚጠቀሙ ከ1 በመቶ በታች 0.95 በመቶ ሲሆኑ በቁጥር ሲቀመጥ 839 ሺህ 580 ኢትዮጵያውያን የፌስቡክ ተጠቃሚ ናቸው ። ከቀደመው ...

Read More »

አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ካቢኔ አያዋቅሩም ተባለ

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሟቹ የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር እግር የተተኩት ጠ/ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አዲስ ካቢኔ እንደማያዋቅሩ ለኢህአዴግ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ጠቆሙ፡፡   ምንጮቹ  አዲስ ካቢኔ የማይዋቀረው በምርጫ አሸንፎ የመጣ አዲስ ጠ/ሚኒስትር ባለመኖሩ ነው ብለዋል፡፡ አቶ ኃለማርያም በአቶ መለስ እግር የተተኩ በመሆናቸው አዲስ ካቢኔ ለፓርላማ አቅርበው የሚያጸድቁበት ምንም ምክንያት የለም ብለዋል  ምንጮቹ፡፡   በዚህም ምክንያት የካቢኔ ሹም ...

Read More »

በሽብር ወንጀል ተከሰው በእስር ላይ በሚገኙት 31 ሰዎች ላይ የክስ መቃወሚያ ቀረበ

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-አቃቢ ህግ በእነ ኡስታዝ አቡበክር አህመድ መዝገብ በሽብርተኝነት በተከሰሱት የድምጻችን ይሰማ የኮሚቴ አባላት ላይ ያቀረበው ክስ ህገመንግስቱን የጣሰ ና በርካታ የህግ ድንጋጌዎች ግድፈት ያለበት መሆኑን በዝርዝር በመጥቀስ ነው፣ የተከሳሾች ጠበቆች ተቃውሞአቸውን ለፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረቡት። ጠበቆቹ 7 ገጾች ያሉት ህገመንግስቱን የተመለከቱና 24 ገጾች ያሉት ዝርዝር መቃወሚያዎችን አቅርበዋል። በተከሳሾች ...

Read More »

በአላማጣ ታፍነው የተወሰዱ ከ20 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በራያና አዘቦ ፣ በአላማጣ ከተማ ከኤልክትሪክ መስመር መቃጠል ጋር በተያያዘ በጥርጣሬ የተያዙ ከ20 በላይ ግለሰቦች ወደ ማይጨው ከተማ ተወስደው መታሰራቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ቢናገሩም ፣ ዘመዶቻቸው እንዳይጠይቋቸው በመደረጉ ስለደህንነታቸው ሁኔታ ለማወቅ አልተቻለም። ወጣቶች የታሰሩት ለኢንቨስተሮች ተብሎ የተዘረጋውን የኤልክትሪክ ምሰሶ አቃጥላችሁዋል በሚል ነው። የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጡት ታፍነው የተወሰዱት ወጣቶች በእስር ቤት ጉዳት ሳይደርስባቸው ...

Read More »

በአድዋ ከተማ አደባባይ ላይ ተሰቅሎ የነበረ የ አቶ መለስ ፎቶ ተቀዳዶ ተጣለ-የራስ አሉላ አባ ነጋ ት/ቤት ስያሜ በአቶ መለስ ስም ተቀየረ

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭  ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በትግራይ ክልል  በአድዋ ከተማ አደባባይ ላይ ተሰቅሎ የነበረ የአቶ መለስ  ዜናዊ ፖስተር ተቀዳዶ ተጣለ ኢየሩሳሌም አርአያ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው በሁኔታው የተበሳጩት የክልሉ ካድሬዎች ለተፈ}መው ድርጊት ጣታቸውን ወደ አረና ለትግራይ ፓርቲ ቀስረዋል። የህወሀት ካድሬዎቹ፦« የመድረክ ተለጣፊ የሆነው አረና ፓርቲ ነው ይህን የፈፀመው » በማለት ያልተጨበጠ የፈጠራ ወሬ እያሰራጩና በድርጅቱ ላይ  እየዛቱ ነው። የዜናው ...

Read More »

የአውሮፓ ገበሬዎች ወተት በአውሮፓ ህበረት ህንጻዎች ላይ በመርጨት ተቃውሞአቸውን ገለጹ

ህዳር ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ገበሬዎቹ ተቃውሞአቸውን የገለጹት የወተት ወጋ በመውደቁ ነው። በሺዎች የሚቆጠሩ ገበሬዎች ፣ በርካታ ትራክተሮችን በማሰልፍ የቤልጂም ዋና ከተማ በሆነችው ብራሰልስ ተመዋል። የወተት ወጋ 25 በመቶ እንዲጨምር የጠየቁት ገበሬዎቹ የአውሮፓ ህብረት ህንጻዎችን በወተት በመርጨት ነጭ አድረገዋቸዋል። የአውሮፓ ገበሬዎች ገበያው ሊሸከመው ከሚችለው በላይ የወተት ምርት የሚያመርቱ በመሆኑ ህብረቱ በየአመቱ ከ47 ቢሊዮን ዩሮ በላይ በማውጣት ለመደጎም ተገዷል።

Read More »

ከሀላፊነታቸው ተነስተው የነበሩት ጄነራል ሞላ ተመለሱ

ህዳር ፲፯ (አስራ አምት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ብወዛ ለማድረግ ከላይ የተጀመረው እንቅስቃሴ ሳንካ እንደገጠመው የመከላከያ ምንጮች ገለጡ። በሜጀር ጀኔራል ማህሪ ዘውዴ እንዲተኩ የተወሰነባቸው የአየር ሀይል አዛዥ ሜጀር ጄነራል ሞላ ሀይለ ማሪያም ተመልሰው ስፍራቸውን መያዛቸውን የአየር ሀይል ምንጮች ገለጸዋል። የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው ለህዝብ ከመገለጹ በፊት በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ሲካሄድ ...

Read More »